Tuesday, 6 June 2017

አዝማሪ ትዝታው የራሱንና የቤተሰቡን የአንገት ማዕተብ ከበጠሰ ቆየ ።

ግሪሳ ትዝታው ( ሉንጎ )  መቅሰፍት ሊወርድበት  ነው
Image may contain: 4 people, people smiling, outdoor

★ ★ ★
 Share ~ Comment ~ Like ~ Tag
★ አዝማሪ ትዝታው የራሱንና የቤተሰቡን የአንገት ማዕተብ ከበጠሰ ቆየ ።
★በኮሎራዶ.! አለ ነገር.! የሚሰማ.! የሚነገርም አለ ነገር ።
 በጀመሪያ መልእክቱን በደንብ አንብቡትና በኮመንት ገባ ገባ በሉላቸው!!
★ እንዲህ ያለውን ጦማር Share ~ Share  ማድረግ በፀረ ተሃድሶው ትግል እጅግ ወሳኝ ነገር ነው ። መረጃው ብዙ ሰው እጅ ገብቶ የመወያያ አጀንዳ ይሆናል ፣ ብዙዎችንም ያነቃል ፣ ጥንቃቄም እንዲወስዱ ያደርጋልና ነው። Comment መስጠትም ሌላው ወሳኝ ነገር ነው ። ደግሞ አስተያየት ስትሰጡ አትልመጥመጡ ፣ አትቅለስለሱ ፣ ወንድ ወንድ የሚሸት አስተያየት ስጡ ።
★ ሚሊዮኖች የእኔን ፔጅ ያነባሉ ፤ በተለይ አገልጋዮችና ወግ አጥባቂ ምዕመናንን እንደ ጉድ ያነቡኛል ። ነገር ግን ጦማሩን ሼር አያደርጉም ፣ ኮመንት አይሰጡም ። ምክንያት ሲባሉ " ዘመዴ በጽሑፎቹ ውስጥ ግሪሳ ፣ በጥራቃ የሚል ቃል ስለሚጠቀም አናደርገውም ይላሉ ። እነዚህ አስመሳዮች ናቸው ። እርቃኗን የቆመች ሴት ፎቶ ሼር እያደረጉ የእኔ ግሪሳ የሚል ጽሑፍ ዘገነናቸው ። እነዚህ የፌስቡክ ላይ ክርስቲያኖች ፣ ናቸው ። የፌስ ቡክ ላይ ጧሚ ፣ ጸሎተኛና ትሁቶች ። እናም እንኳን ሼር አለማድረግ አይደለም ለምን ሳያነቡት አይቀሩም ። ምድረ በጥራቃ ሁላ.!!!
አሁን ወደ ግሪሳው አዝማሪ ትዝታው( ሉንጎ ) ዜና እናልፋለን ። መልካም ቆይታ.! ።
......በመጀመሪያው የ1997 ዓም ምርጫ ወቅት የፖለቲካው ትኩሳት በጋመበት ሰዓት አዲስ መንግሥት ይመጣል በሚል ተስፋ በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ እያለ እሱን ራሱን ሉንጎን ጨምሮ 11 ልጆች በመሆን ኢህአዴግን በመቃወም ለቅንጅት ድጋፍ በመስጠት ፤ በድፍረት የወያኔን አገዛዝ በመቃወም ለተባበሩት መንግሥታት ፣ ለአፍሪካ ኅብረት ፣ ለአረብ ሊግ ፣ ለአሜሪካና እንጊሊዝ መንግሥታት ሳይቀር የተቃውሞ ደብዳቤ ካስገቡት ግለሰቦች መካከል የነበረ ግለሰብ ነው ። ትዝታው ( ሉንጎ)
እኔ ራሴን ጨቅጭቀውኝ ድርጅቴ ድረስ በመምጣት " ዘመዴ!! "ኢህአዴግን ተቃውመን መግለጫ የምንሰጥበት ሚዲያ ፈልግልን ባሉኝ መሠረት በወቅቱ ተነባቢ ጋዜጣ የነበረችውን " ነፃነት " የተባለችው ጋዜጣ ላይ መግለጫ እንዲያወጡ ጋዜጠኛ " ደረጀን በመጥራት ኦዳ ራመት በተባለ ሆቴል ውስጥ በግዋሻው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዲሰጥ አስደርጌው ነበረ ። በወቅቱ ከ" ንክር ፋራና ሰገጤ የገጠር ልጅነት በመውጣት በዝግመተ ለውጥ ወደ አራድነት መጠጋት የጀማመሩበት ወቅትም ስለነበር " እርዳን አግዘን " ባሉን ነገር ሁሉ ሳግዛቸው ነበር ።
የቅንጅት አሸናፊነት ሲከሽፍ እነ ትዝታው ሉንጎ ከመንፈሳዊ ኮሌጅ በደብዳቤ ተባረሩ ። ወዲያውም የሚበሉት ሲያጡ በአዋሽ ባንክ አካውንት ከፍተው እርዳታ መለመን ጀመሩ ። የሚገርመው የባንክ አካውንቱ እስከዛሬ አልተዘጋም ። የዚህን ጊዜ ነው ኢህአዴግን መቃወም እንጀራ እንደሚያስገኝ የተረዱት እነ በግዋሻው ወዲያውኑ ከፓስተር መለሰ ወጉ የተገለበጠውን " የመስቀሉ ስር ቁማርተኞች " የምትል አነስተኛ ፓፍሌት መሳይ የመጽሐፍ ስም የተሰጣት ፓፍሌት በማሳተም አገር ምድሩን አንቀጠቀጡት ። መጽሔቷ በበጋሻው ስም ትውጣ እንጂ ትዝታው ሉንጎም የበረሃ ጓዱ ስለነበር ጥቅሙ የጋራቸው ነበር ። በወቅቱ በፓፍሌታ የተናደደው ወያኔ በጋሻውን ይዞ ማእከላዊ አሰረው ።
ያኔ ነው እኔም ጌቱ ከሚባለው የአብ መዝሙር ቤት ባለቤት ጋር በጋሻውን ለመጠየቅ ማእከላዊ ስሄድ የበጋሻውን እናት ለመተዋወቅ የበቃሁት ። የበጌ እናት በንዴት ኒያላ የተባለውን ሲጋራ በላይ በላዩ እያጨሱ " ተው ብዬህ ነበረ ። አልሰማ አልከኝ ፣ ውቃቢዬ አውሊያዬ ነግሮኛል ። እረፍ ብዬህ ነበር እያሉት ሲቆጡት የደረስኩት " የበጌ እናት በለአውሊያ መሆናቸውን እና በቤታቸው ለብዙዎች የሚፈርዱ በለዛር ሴት መሆናቸውን የዚያን ቀን ነበረ በአይኔ ያየሁት በጆሮዬም የሰማሁት ። አቤት በግዋሻው እንዴት እንደአበደ ። " ማን ጠይቂኝ አለሽ? ፣ ማን ነይ አለሽ? ፣ ሁለተኛ አትምጪብኝ እያለ ሲያለቃቅስ አሳዘነኝ ። እናቱን እንኳ ከአጋንንት አሰራር አውጥቶ ወደ ህይወት መንገድ ያልመለሰ ሰባኪ ያውም ሳይማር መጋቤ ሀዲስ የሚባል ማዕረግ የተሸከመ ፍልጥ እና ዥልጥ ያለ " ሀ " ገደሉ የሆነ ሰው ነው እንግዲህ ሌሎችን አስተምሬ መንግሥተ ሰማያት ካላስገባሁ ሞቼ እገኛለሁ የሚለው በጥራቃ ።
እንግዲህ ከዚህ ከማዕከላዊ እስር በኋላ ነው በግዋሻው ከተቃውሞ ትእቢቱ ተንፍሶ በመውጣት ከመቅስፈት ትዝታው ሎንጎን ጨምሮ ብዙዎቹ የደኢህዴን ኢህአዴግ ደጋፊና አባል ለመሆን የበቁት ። ሉንጎ ከመናፍቁ " አባ " ሰረቀ ጋር በመሆን ከኢህአዴግ የተሰጣቸውን ተልእኮ ለማስፈፀምና ማኅበረ ቅዱሳንን የማፍረስ ፕሮጀክት ከበጋሻው ጋር ሓለፊነት ወስዶ ይንቀሳቀስና እንዲንቀሳቀስ የተደረገ ግለሰብ ነበር ።
የሁሉም መሪና ጠርናፊ ደግሞ በፊት የማኅበረ ቅዱሳን አባል ሆኖ ራሱ ማኅበረ ቅዱሳንን እንዲሰልል ኃላፊነት ወስዶ የነበረውና አሁን በሀገረ አሜሪካ የሚገኘው ቀሲስ ሰሎሞን ሙልጌታ ነበር ። ዱባይ ላይ ቤተክርስቲያን እንዲከፈት ያደረገ ፣ የሚሊንየሙ ጉባኤን ከጀርባ በመሆን ለያሬድ አደመ ትእዛዝ በመስጠት በቤተክርስቲያን ስም ምእመናን ገንዘባቸውን እንዲዘረፉ ያደረገው ግለሰብ ነው ሰሎሞን ማለት ። ይሄው ሰሎሞን ሰሞኑን ዘማሪ ወንደሰን በቀለና ዲን ዳዊትን ይዞ ሲያለቃቅስብኝ መክረሙን አይቻለሁ ሰምቻለሁም ። ወንዴና ዴቭ ፣ አካሉና እስክንድር በጊዜ ሚናችሁን ለዩ ። መረጫጨት ከተጀመረ ለእናንተ ጥሩ አይመጣም ።
በከፍተኛ የስኳር ህመም የሚሰቃየው ግሪሳ ትዝታው (ሉንጎ ) በኢትዮጵያ በተለይ በዲላ ከተማ የማኅበረ ቅዱሳን ቢሮዎችን ለጊዜውም ቢሆን እንዲታሸጉ ያደረገም ግለሰብ ነው ። የድምፅ ቅጂውንም" አርማጌዶን " በተሰኘው ቪሲዲዬ ላይ ተመልከቱት ። እንዲህ እንዲህ እያለ እንደምንም ብሎ በሴት ጀርባ ላይ ተንጠልጥሎ " ገሌ " በመሆን አሜሪካ የገባው ሉንጎ ፤ አሜሪካ እንደገባ ወዲያውኑ የወያኔነት ካባውን አውልቆ የስደተኛውን ሲኖዶስ በመቀላቀል ዋነኛ የወያኔ ተቃዋሚ ሆኖ አረፈው ። በኢትዮጵያ ሳለ እኔን ለመደበቅ ሲል የሟቹን ፓትሪያርክ የአብነ ጳውሎስን ኃውልት አሰሪ ኮሚቴ የነበረ ሰው አሁን ደግሞ በአሜሪካ ከአቡነ መርቆሬዎስ ሥር ተለጥፎ ያሽካካልኛል ። ምደረ አረፊ ፖለቲከኛ ነኝ የሚለውን የድሮ አራዳ ሁሉ ይጫወትበታል ።
አሜሪካን ከገባ በኋላ የውጪውን ሲኖዶስ እንደ መደበቂያ ሽፋን በመጠቀም ያለፉትን ጥቂት ዓመታት በዴንቨር ኮሎራዶ ደግማዊት ግሸን ማርያም ቤተክርስቲያን ውስጥ መሽጎ የስህተት መርዙን በተናጥል በየግለሰቦች ላይ በመዝራት ፤ እሱ ከመምጣቱ በፊት ፍቅር በፍቅር የነበሩትን ግለሰቦች ሆድና ጀርባ አድርጓቸው ቆይቷል ። በተለይ አሁን ቤተክርስቲያኒቱን የሚያስተዳድሩት አባት ጥበብ በተሞላበት አካሄድ ውልፍት እንዳይል ሰቅዘው በመያዝ አላላውስ ብለው በጥበብ ያዙት እንጂ ልጁ ዋና አላማው የቤተክርስቲያኒቱን አስተዳደር በመያዝ የግሪሳዎቹ መፈንጫ ለማድርግ ነበር ዋና ፍላጎቱ ። በዚህ በኩል ቦርዱ ፊት በለመስጠት ያደረገው በጎ ነገር ያስመሰግነዋል ።
የቤተክርስቲያኒቱ ቦርድ በመጀመሪያዎቹ ዓመታት ለግሪሳው ጥብቅና በመቆም ይከራከርለት የነበረ ብቻ ሳይሆን ከ 3500 ዶላር በላይ የደምወዝ እየከፈለው አንደላቅቆ ያኖረው የነበረ ቢሆንም ዘንድሮ ግን አሁን የአሜሪካው ስደተኛው ሲኖዶስ በደብሯ ላይ ስብሰባ ማድረጉን ተከትሎ አጋጣሚውን በመጠቀም የምንፍቅና ሸቀጡን ለማራገፍ በመቋመጥ በይድረስ ይድረስ የተዘጋጀና ከየትኛውም የቤተክርስቲያን ዓውደምህረት ሳትወገዝ የተወገደችውን በመናፍቋ ፓስተር " ዘርፌ " አጃቢነት የቀረበ ቀረርቶ በተከበረችው ደብር ስም ለመሸጥና ዶላር ለማጋበስ ቋምጦ የነበረውን ሉንጎ ያደረገውን አሳፋሪና ፍፁም ስግብግብነት የተመላበት ሙከራ በመመልከት ይህን ሸቃጭ ነጋዴ " ቀረርቶህ በደብራችን ውስጥ አይሸጥም " በማለት ቦርዱ ወሽመጡን በጥሶ ጥሎለታል ።
የቦርዱ ውሳኔ የበጋ መብረቅ ያህል የሆነበትና የደነገጠው ሉንጎም በሁኔታው "ፍዝዝ ፣ ቅዝዝ " ከማለትና ጨጓራዬን አመመኝ ብሎ ከመተኛት ውጪ ምንም ምላሽ ያልነበረው ሲሆን የትዝታው ባለቤት ግን ጨርቋን ጥላ ፤ አቅሏንም ስታ ማበድ እስኪቀራት ድረስ ያዙኝ ልቀቁኝ ፣ ምን ሲደረግ ነው የአዝማሪው ባሌ ቀረርቶ የማይሸጠው በማለት አዋራ ስታስነሳ እንደነበር ታይታለች ። ከምር በእጄ የገባውን ቪድዮ ሳይ አሳዘነችኝ ። ለቅዱሳን ክብር አይገባም በማለት ማኅተባቸውን የበጠሱት ባልና ሚስቱ ቤተክርስቲያንን የሚፈልጓት " ለሸቀጥ ማራገፊያነት " ነውም ተብሏል ።
አሁን ከትዝታው ጎን የቆሙት ጥቂት ቤቢ ሲተሮችና የቤተክርስቲያኒቱ ቦርድ ውስጥ ካሉት አባላት መካከል አንዲት ሴት ስትሆን ፤ በተለይ ሴትየዋ በቦርድ ደረጃ የተነጋገሩትን ይዛ በመውጣት ለሉንጎ በመንገር እሱም አድማ የሚመቱ ቤቢ ሲተሮችን በማዘጋጀት እስከአሁን ሲንቀሳቀስ ቆይቷል ። አሁን ግን በትዜ ላይ ጀንበር የጠለቀች ይመስላል ። የሚገርመው ነገር ደግሞ ሴትየዋ ይህን አይነት ድጋፍ ስትሰጠው ባለቤቷ አቶ ታረቀኝ ደግሞ ከቅድስት ቤተክርስቲያን ጎን የቆመ መሆኑ ነው ።
የሚገርመው ነገር የአሜሪካው ሲኖዶስም በዘንድሮው ስብሰባው በማጠቃለያው ላይ በሰጠው ውሳኔ በ6 ተኛው ተራ ቁጥር ላይ " ተሃድሶ የሚባል አዲስ ሃይማኖት መጥቷልና " ተጠንቀቁ በማለት በድፍረት ሲናገር ተደምጧል ። ተሃድሶ የሚባል የለም ባዩን ግሪሳ ትዝታውን በተቀመጠበት ውኃ የቸለሰበት ውሳኔ ሲሆን ፣ በአንፃሩ ደግሞ ተሃድሶ ያስፈልጋል ባዮቹን አባ ወልደትንሳኤንና አባ ገብረሥላሴን ጳጳስ አድርጎ በመሾም ፣ እነ ልኡለቃልን ፣ እነሽታ ቡዝዬን ፣ እነ እንዳልካቸው ዳኘውንና ፣ እነ ፓስተር መላኩን አዝሎ እየዞረ ስለ ተሃድሶ ቢያወራ ሰሚ የሚያገኝም አይመስልም ። እርግጥ ነው ፤ ይፋ አይውጣ እንጂ በዘንድሮው ስብሰባቸው " ለአባ ወልደትንሣኤ አያልነህ " ከባድ የተባለ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ውስጥ ውስጡን ይወራል ። ለዚህም ነው በዴንቨሩ ስብሰባ አባ ወልዴ ድምጻቸውም መልካቸውም ድራሹ የጠፋው የሚሉ ሰዎች የበዙት ።
አሁን ለምድረ ተሃድሶ ሁላ አሜሪካ ውስጥ ይሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የትም ይሁን የት በሁሉም ቦታዎች መንገዶች ሁሉ ዝግ ሆነውባቸዋል ። የሚያስተምሩበት መድረክ ተነጠቀዋል ። እሰከ ዛሬ ያለ ከልካይ ሸቀጣቸውን ያራግፉበት የነበረው ዓውደምህረት ዝግ ሆኗል ። የትዝታው ዘፈን በራሱ በፕሮቴስታንቶችና የንግድ ድርጅቶች ውስጥ በይፋ መሸጥ ተጀምሯል ። ዴንቨር ኮሎራዶ የፕሮቴስታንቶች ጸጉር ቤት ውስጥ ለሽያጭ መቅረቡ ታይቷል ። እናም አሁን ሁሉም ባንኗል ። ያልባነነው ደብሯ የቦርድ አስተዳደር ብቻ ነው ።
ወይዘሮ ስፍነ የሰንበት ትምህርት ቤቱ ሊቀንበር ናት ። የትዝታውም ድብን ያለች ቲፎዞም ነበረች ። ኋላ ላይ ግን እየቆየች ስትመጣ ነገር ዓለሙ ሁሉ ተገለጠላት በተለይ የእመቤታችንን መዝሙር እንዲዘምር ፤ ልጆቹንም እንዲያስጠና የምትመክረውን ምክር ባለመስማት ለእመቤታችን አልዘምርም ካላት ጊዜ ጀምሮ በአንድ ጊዜ እሳትና ጭድ ሆነው ከርመዋል ።
አሁን ያበጠ ነገር የሚፈነዳ ያለ ይመስላል ። በውስጥ መስመር ከደብሯ እንደሚደርሱኝ መረጃዎች ከሆነ የደብሯ የበላይ ጠባቂ አቡነ ናትናኤል የተባሉት አባት ሉንጎን ጉድ ሳርተው መላው ዓለም ላይ የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያንን ጮቤ ያስረግጣሉ እየተባለም ነው ። ሉንጎ ሉቡ ተራራ ነው ። ከደብሯ ቢባረር ጥቂት የደቡብ ልጆችና ቤቢ ሲተሮች ቢከተሉት እንጂ እሱን ተከትሎ የሚወጣ አንድም ሰው አይኖርም ።
የመረጃ ምንጮቼ እንደሚሰጡኝ መረጃ ከሆነ የቤተክርስቲያኒቱ ሽማግሌዎች እጅግ ጠንካራ ሽማግሌዎች መሆናቸው ይነገርላቸዋል ። በሃይማኖት ቢሉ በሀገር ፍቅር የሚታሙ አይደሉምም ይባላል ። እነ አቶ ጥላሁን ፣ ዲን ዮሴፍ ፣ አቶ ታሪኩ ፣ አቶ ሞላ ፣ አቶ ባዬ ፣ አቶ ናርዶስ ፣ አቶ ዳዊት ፣ አቶ ለገሰ ፣ ወጣት ነብዩ ፣ አቶ ለይኩን ፣ አቶ ኤፍሬም እና ዶር አሰፋን ፣ የያዘው ቦርድ እስከዛሬ ክፉ ደጉን አብረው ያሳለፉትን ምእመናን ብሶትና ሮሮ ሳይሰማ ጆሮውን ደፍኖ ለአንድ ተራ መናፍቅና ፀረ ማርያም ወንበዴ ጥብቅና በመቆሙ ብዙዎች ሲያዝኑ ኖረዋል ። አሁን ግን አለ ነገር እየተባለ ነው ።??? አለ ነገር.??
በመጨረሻም አዝማሪ " ትዝታው" ከዚህ በፊት እኮ ለእመቤታችን ዘምሯል ፤ እንዲያው ምን ነክቶት ነው ብለው ለሚሟገቱ " ምስኪኖች " አዎ ዘምሯል ። ምልጃዋንም አሳምሮ ዘምሯል ይሄ ሁሉ እውነት ። ነገር ግን አሁን አዝማሪው የእመቤታችንን ስም ማንሳት እንደነውር መቁጠር ከጀመረ ቆየ ። በፊት ስለ እመቤታችን ዘመረ ከተባለው ቀረርቶ መካከልም እስቴ አንዱን ጋብዣችሁ እንሰነባበት። "
ወደስኒ ካልሽኝማ " ።
★★ ★
ወድሰኒ ከልሽኝማ
አመስግነኝ ካልሽኝማ
ይልና አዝማሪ ትዝታው ፤ እንዲህ ይደረግ ፤ ምስጋና አምሮኛል ካልሽኝ ፤ መመስገኑንም ከፈለግሽ ፣ እናም ካስቸገርሽኝ ፤ የግድም ብለሽ ወጥረሽ ከያዝሽኝ ፣ ጭቅጭቅም ካደረግሽኝ እንግዲያው እኔ እንዳመሰግንሽ በቅድሚያ ማሟላት ያለብሽን ልንገርሽ ይላታል ደፋሩ ሉንጎ እመቤታችንን ። ለቅዱስ ኤፍሬም ተደረገ የተባለው እውነት ከሆነና ፤ አሁንም ልክ እንደ ቅዱስ ኤፍሬም እኔም እንዳመሰግንሽ ከፈለግሽ ፦
፩ኛ፤ በደመና ውረጂና
፪ኛ፤ የእሳት አትሮንስ ይዘርጋና
፬ኛ፣ ላመስግንሽ እንደገና ፤
ያለበለዚያ በዚህ ስምምነታችም መሰረት ለቅዱስ ኤፍሬም አደረግሽ የተባለው ነገር የማይደረግ ከሆነ ስለአንቺ የመዘመር ግዴታ የለብኝም ነው " ፈረንሳይኛው " ።
እናንት የእናት ጡት ነካሾች የገባችሁበት ብትገቡ አልፋታችሁም ። አይደለም አሜሪካ ጠፈር ላይ ብትወጡ እንዲሁ በዋዛ አልለቃችሁም ። ንስሃ ትገቡ እንደሁ ብዬ በብርቱ ጠበቅኳችሁ እናንተ ግን ባሰባችሁ እንጂ የሰናፍጭ ቅንጣት ታህል የመጸጸት ነገር አላሳያችሁም ። ስለዚህ አልፋታችሁም ። ምን ያህል በእናንተ ላይ የእናንተን የውስጥ አንጀት ጉበት ገልብጬ ለህዝቡ ለማሳየት ዋጋ እንደከፈልኩ ልባችሁ ያውቀዋል ።
★ ሀገሬን ★ ቤተሰቤን ★ ልጆቼንና ጓደኞቼን አጥቼማ ያለውጤት ዝም ብዬ የምቀመጥ አይምሰላችሁ ። ወዳጄ ትእዛዙ ከላይ ነውና አንላቀቃትም .!! ። የማንንም ድጋፍ አልሻም ። የሲኖዶስ ውግዘትም አልጠብቅም ፤ ረድኤተ እግዚአብሔርን አጋዥ አድርጌ፣ የብርሃን እናት ወላዲተአምላክን ይዤ ፣ በቅዱሳኑ ጸሎትና ምልጃ እየታገዝኩ አፈር ከድሜ ማስጋጥ እንደሁ አያቅተኝም ። ሲያዩዋችሁ ለተመልካች ጎልያድ ብትመስሉም እናንተን አጋድሞ ከ " ተዋሕዶ " ትከሻ ላይ ለማራገፍ የዳዊት ጠጠርና ወንጭፉ በቂ ነው ። አለቀ ። አራት ነጥብ ።
ማሳሰቢያ.! በውጪው ሲኖዶስ ሥር ለምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች በሙሉ ። ወያኔም መውደቁ ፣ አንድ ቀን ታሪክ መሆኑ አይቀርም ። በወያኔ አኩርፋችሁ እንጂ እምነታችሁ ያው የጥንቱ የጥዋቱ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ መሆኗ ይታወቃል ። ነገ እግዚአብሔር ሲፈቅድ ፤ በቃችሁ ሲለንም አንድ መሆናችን አይቀርም ። ጊዜው ሩቅ እንዳይሆን መጸለይም አለብን ። እናም ገና ለገና እላይ ያሉት የሃይማኖት አባቶች ተጣልተዋል ፣ የሚታረቁም አይመስልም በሚል ሰበብ የማንም ልቅምቃሚ መናፍቅ መጫወቻና መጠራቀሚያ መሆን የለባችሁም ። ተአምረ ማሪያም የማያነቡ ፣ ሴቶችን ታቦት ማየት ትፈልጋላችሁ ወይ እያሉ በድፍረት ከመንበሩ ላይ ወስደው ለማሳየት የሚሞክሩ ፣ በሥጋወ ደሙ የሚያላግጡ ፣ ሴቶችን ታቦቱ ያለበት መንበሩ ድረስ አስገብተው ጽዳት እንዲያፀዱ የሚያደርጉ ግልፅ መናፍቅ የሆኑ ግለሰቦችን ልትቃወሙ ይገባል ። የምንለያይባቸው ብዙ ሀገራዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ቢኖሩም በእምነታችን ግን አንድ ነን ። እናም በአንድነት እንታገላቸው ።
እነዚህ ሰዎች በጣም ብዙ አይደሉም ፣ ነገሩ ነጭ ልብስ ላይ እንዳረፈ ጥቁር ነጥብ ሆነው ጎልተው ይታያሉ እንጂ ብዙ አይደሉም ። ከፈለጋችሁ በፎቶ አሳያችኋለሁ ። ከእነዚህ ሰዎች ራቁ ። በእውነት ራቁ ብያለሁ ። የኢትዮጵያ አምላክ ለእነዚህ አጥፊዎች የእጃቸውን ይሰጣል ፣ እንዲህ አምናለሁ ። እንዲህም እታመናለሁ ። ለዛሬ አበቃሁ ።
በቀጣይ የዘርፌን ወቅታዊ ሁኔታና ያለችበትን አሳዛኝ ህይወት እንመለከታለን ። አከተመ ።
"ግን እላለሁ !!! እምዬ ኦርቶዶክስ አንቺ እናትዓለም ፤ የእነ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ፣ የእነ ቅዱስ አትናቴዎስ እና ቅዱስ ቄርሎስ የእነ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፣ የእነ ቅድስት አርሴማ ፣ የእነ አቡነ ተክለሃይማኖት ፣ የእነ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ፣ የአባ ሳሙኤል ዘዋልድባና የአቡነ አረጋዊ ሃይማኖታቸው የሆንሽ ንጽህት ተዋሕዶ ሃይማኖቴ ሆይ ! ብረሳሽና ብከዳሽ ቀኜም ትርሳኝ፣ ትክዳኝም ። ባላስብሽና ባልሞትልሽ ምላሴ ከጉሮሮዬ ይጣበቅ ። ሳለጎበድድና ሳለከዳሽ እንድኖርም አምላክሽ ይርዳኝ ። ይህን ባለደርግና ሳልጮህልሽ ዝም ብዬ ብሞት ፤ ስሜ ከህይወት መጽሐፍ ይደምሰስ ።
"ጌታ ሆይ! ከዚህ በፊት በሆነው ፤ አሁንም እየሆነ ባለው ነገር እና ወደፊትም በሚሆነው ሁሉ ፤ ክብሩን አንተ ውሰድ ።" አሜን. !
"ድንግል ሆይ እናቴ ! አዛኝቱ ዛሬም እንደትናንቱ ቅደሚ ከፊት ከኋላዬ "
ይህንንም ራሴው በእጄ ጻፍኩት ። +4915217428134 ደግሞ የቫይበር ፣ የኢሞና የኋትስአፕ መልእክቶችን የምቀበልበት የእጅ ስልኬ ነው ።
ሻሎም.! ሰላም.!
ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
ግንቦት 27/2009 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ ።

የተከበረው የመቅደሳችን ስፍራ በሁለቱ ኃይለማርያሞች ተደፈረ ።

Image may contain: 8 people, people standing and indoor
★★★
የተከበረው የመቅደሳችን ስፍራ
በሁለቱ ኃይለማርያሞች ተደፈረ ።

" እንግዲህ በነቢዩ በዳንኤል የተባለውን የጥፋትን ርኩሰት በተቀደሰችው ስፍራ ቆሞ ስታዩ፥ አንባቢው ያስተውል፥" ማቴ 24፣15
በዚህ ፖስት ላይ ገብቶ የሚንበጫበጭ መናፍቅ Block በተባለው ሰይፌ ይቀጣል ። አራት ነጥብ.! ።
 Share ~ Share ~ Share ~ Comment.
★ደፋሪዎቹ አንዱ መነኩሴ አንዱ ጠቅላይ ሚንስትር ናቸው ።
★ደፋሪዎቹ አንዱ በኢትዮጵያ አንዱ በኢየሩሳሌም የሚገኘውን መቅደሳችንን ነው የደፈሩት ።
★ ይሄ ሁሉ ሲደረግ ቅዱስ ሲኖዶሳችን ደክሞት ለሽሽ ብሎ ተኝቶልናል ። አትቀስቅሷቸው ፣ አትረብሿቸው ። ይተኙበት ፣ ይረፉበት ።


..... ነቢየ እግዚአብሔር ኤርሚያስ እንዲህ ይላል ።" የመቅደሳችን ስፍራ ከጥንት ጀምሮ ክፍ ያለ የክብር ዙፋን ነው። " ኤር 17፣12 ። አዎ እውነት ነው የመቅደሳችን ሥፍራ ከጥንት ጀምሮ ከፍ ያለ የክብር ዙፋን ነው ። አሁን ግን ይህ የክብር ዙፋን የሆነ ሥፍራ በዘመናችን ከኢትዮጵያ ማኅፀን በበቀሉ ጉደኞች የተነሳ ከጥንት ጀምሮ ከፍ ያለው የክብር ዙፋን የሆነውን መቅደሳችንን በሚያረክሱ ጉደኞች ተወርሯል ።
ደክተር አባ ኃይለማርያምና ፓትሪያርክ አባ ማትያስ በአዲስ አበባ የሰዓሊተ ምህረት ቅድስት ድንግል ማርያምን ቤተክርስቲያን እንዲደፈር ሲያደርጉ ፤ በኢየሩሳሌም ደግሞ እነ አባ ፍስሐ ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ከሚስቱና ከአምባሳደሩ ከውጭ ጉዳይ ሚንስትሩና ከሚንስትር ደኤታዎቹ ጋር ከፍ ያለውን መቅደሳችንን በጫማ ጠቀጠቁት ። ይሄ ንቀት ነው ። ይሄ ድፍረትም ነው ። ምን ታመጣላችሁም የሚል መልእክት ማስተላለፋቸውም ነው ።
አሁን ሌላው ድፍረት የተፈጸመው በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም የሚገኘው ዴር ሱልጣን የኢትዮጵያ ገዳም ውስጥ ሲሆን የድፍረቱ ፈፃሚ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዩ ጠቅላይ ሚኒስቴር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ነው ። ጠቅላይ ሚንስትሩ ከነጫማው በመግበት ቅድስት የተዳፈረው መቅደሳችን ደግሞ በዴር ሱልጣን ውስጥ ከሚገኙት ሁለት ቤተ መቅደሶች መካከል አንደኛው በሆነው በአርባዕቱ እንሰሳ የመድኃኔአለም ቤተ ክርስትያን ውስጥ ነው።
ቦታው የቱሪስቶች መተላለፊያ ቢሆንም መቅደሱ ውስጥ ያውም ምንጣፉ ላይ እንዲህ በድፍረት ከነጫማው መንግሥቱ ኃይለማርያምም ቆመ የሚል አልሰማሁም ። አላነበብኩምም ።
እንደ አንድ የዚህች ታላቅ ሀገርን የመምራት እና አጋጣሚውን የማግኘታቸው ይህን የኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን የመላው ዓለም ኩራት የሆነን ገዳም መጎበኘት መብትም ግዴታውም ነው ። በዚያ ያለውን የገዳሙን አስከፊ ይዞታ በመጎብኘት ለመፍትሄው ከግብፅና ከእስራኤል መንግሥታት ጋር ተነጋግሮም ለመፍታትም ቢሞክር ቢያስመሰግነው እንጂ አያስወቅሰውም ። ነገርግን የሚጎበኘው ገዳም ህግና ስርዓት መከበር አለበት ።
በገዳ ስርዓት ላይ ተገኝቶ ቡሉኮ መልበሱ ። በሀረሬዎች በዓል ላይ ተገኝቶ የእስላም ቆብ ማጥለቁ ፣ ትግራይም ጎንደርም ተገኝቶ የአካባቢውን ማኅበረ ሰብ ባኅል እንደሚያከብር ያሳየ መሪ ። እንዴት ዛሬ የተከበረውን መቅደሳችንን እንዲህ በጫማው ከእነ ሚስቱ ሊጠቀጥቀው ድፍረት አገኘ ።??? ፕሮቴስታንት መሆኑን አሳይቶ ኦርቶዶክስን ለማዋረድ ፈልጎ ከሆነ በፍፁም ተሳስቷል ።
ልብ እንበል.! እነ አሰግድ ፣ እነ በጋሻው ፣ እነ ያሬድ አደመ የሚደገፉት በእነዚህ ሰዎች ነው ። አከተመልን ።
አሁን ይህንም ፖስት አይቶ የፓርቲው ክብር ከእግዚአብሔር ክብር የሚበልጥበት ፤ እኔንም ዘረኛ ፣ ምናምን የሚለኝ ጉደኛ አይጠፋም.!!
እናም ይህን ሁሉ ድፍረት ባየን ጊዜ ልክ እንደ መዝሙረኛው ዳዊት እንዲህ እያልን ወደ እግዚአብሔር እንጮሃለንለን ።
1፤ አቤቱ፥ አሕዛብ ወደ ርስትህ ገቡ፤ የቅድስናህንም መቅደስ አረከሱ፥ ኢየሩሳሌምንም እንደ መደብ አደረጉአት።
. . .
4፤ ለጎረቤቶቻችንም ስድብ ሆንን፥ በዙሪያችንም ላሉ ሣቅና ዘበት።
. . .
10፤ አሕዛብ፥ አምላካቸው ወዴት ነው? እንዳይሉ፥ የፈሰሰውን የባሪያዎችህን ደም በቀል በዓይኖቻችን ፊት አሕዛብ ያወቁ፤
. . .
12፤ አቤቱ፥ የተዘባበቱብህን መዘባበታቸውን ለጎረቤቶቻችን ሰባት እጥፍ በብብታቸው ክፈላቸው።
ጠቅላይ ሚንስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ ነው ። ባለቤቱም ወይዘሮ ሮማን እንደዚያው ። በእውነት አቶ ኃይለማርያም መስጊድ ቢገቡ እንዲህ በድፍረት ይገቡ ነበርን.?? ወሮ ሮማንስ ሰዐውዲ አረቢያን ቢጎበኙ እንዲህ ሆነው ተገላልጠው በድፍረት ከነጫማቸው በቤተመቅደስ ይታዩ ነበርን. ???
አቶ ብርሃነ ፣ አምባሳደሩ አቶ ፣፣፣፣ የውጭ ጉዳይ ሚንስተር አቶ ወርቅነህ ገበየሁ ፤ ሦስቱም ጥብቅ ሃይማኖተኛ ከሆነው ከትግራይ ሕዝብ ማኅፀን የፈለቁ ሰዎች ናቸው ። እናም ምን ይሰማችሁ ይሆን እንዲህ ኦርቶዶክስን ስታዋርዱ ።
ለነገሩ.! አቶ ስብሐት ነጋ በግልፅ ተናግረዋል ። ቀደም ብለውም ነግረውናል ። የኦርቶዶክስ ሃይማኖትና የአማራውን የጀርባ አጥንት አድቅቀን ሰብረነዋል ።
ይሄው እየሰበሩት ነው ።
በአዲስ አበባ በሰዓሊተ ምሕረት ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተመቅደስ ውስጥ ፓትሪያርክ አቡነ ማትያስና ዶር አባ ኃይለማርያም መቅደሳችንን በእምነት በማይመስሉን ሰዎች እንዲደፈር አደረጉ ። መቅደሳችን በመናፍቃን ጫማ ተጠቀጠቀ ፣ ንዋየተ ቅዱሳኑ ወጥተው በሴት ፓስተሮች ጭምር እንዲባረኩ ተደረገ ። እናም እኛም ብንጮህ ሰሚ የለም ሳንል ይኸው እስከዛሬ እንጮሃለን ።
አሰግድ ሳህሉ በቅዱስ ሲኖዶስ ቢወገዝም ፤ የውግዘቱ ደብዳቤ በቅዱስ ፓትሪያርኩ አንደበት ተነብቦ በመላው ዓለም ለሚኖሩ ክርስቲያኖች በቴሌቭዥን ቢታይም " አቶ አባይ ፀሐዬ " ማን አባቱ ነው የሚያወግዘው ብለው በነፃነት ፤ ጥበቃ ተደርጎለት እንደልቡ እንዲፊነጭ ማድረጋቸው ነው እየተነገረ ያለው ። እንዲያውም ከዚህም በላይ ፓስተር አሰግድ በመንግሥቱ ድጋፍ የ24 ሰዓት የቴሌቭዥን ፕሮግራም በናይል ሳት ከመጪው ሐምሌ አንድ ጀምሮ ሊጀምር እንደሆነ በይፋ ተናግሯል ።
ይህ ሁሉ ሲሆን በተለይ በሥርዓቱ ውስጥ የምትገኙ ለትግራይ ልጆች መልእክቴ በቅንነት ይድረሳችሁ ።
መቀሌ በተሃድሶ እየታመሰች ነው ። አዲግራት ምን አይነት ጭንቅ ውስጥ እንዳለች በነገው እለት በምለቀው ፖስት ማየት ትችላላችሁ ፣ ሽሬዎች ከተሃድሶ ጋር የሞት ሽረት ትግል ውስጥ መሆናቸው የሚታይ ነው ። አክሱም የችግር ጭምጭምታ እየተሰማ ነው ። አሁንም ይህ ሁሉ እየሆነ እያያችሁ የፓርቲ ፍቅር ከሀገርና ከሃይማኖት በላይ ሆኖባችሁ ፤ ውስጣችሁ እየሆነ ባለው ነገር ማረሩ እያስታወቀ በተግባር ግን ጥፋቱን እያጠፉ ያሉት ከፓትሪያርኩ ጀምሮ እስከ የመንግሥት የሥልጣን ስፍራ ያሉት የሀገራችሁ ልጆች የሚፈፅሙትን ድፍረት የተሞላበት ድርጊት እያያችሁ ዝምታን በመምረጣችሁ ስለ እውነት ከልብ አዝናለሁ ።
እንዲያውም ከዚህ በከፋ ሁኔታ በስመ ደኅንነት ለአሰግድም ሆነ ለውርጋጡ ከፍ ያለው ቱፋ የጥበቃ አገልግሎት እየሰጡት ጭምር መሆኑን ስናይ እኔ በበኩሌ እጅግ አድርጌ አዝናለሁ ።
ኢትዮጵያንም ሆነ ተዋሕዶን የሚታደግ እግዚአብሔር ነው ። አሁን ጊዜው በሰጣችሁ ሁሉን የማድረግ ስልጣን ተጠቅማችሁ ሀገሪቱንም ሆነ ቅድስት ቤተክርስቲያንን መታደግ ስትችሉ ፤ነገር ግን በቸልተኝነት ፣ በፍርሃት ፣ በይሉኝታ ተሸብባችሁ ዝም ብትሉ የቅድስት ቤተክርስቲያን አምላክ ይፋረዳችኋል ። ከፍያለው እንኳ ከአቅሙ ሽጉጥ ታጥቆ እንዲዞርና ለዘመድኩን መረጃ የሚሰጠውን አካል ባገኘው እደፋዋለሁ እያለ እንዲፎክር የልብ ልብ ስትሰጡት ሳይ አፈርኩባችሁ ።
በአኔ እምነት ሀገሬንም ሃይማኖቴንም የሚታደግ ሰው እግዚአብሔር ሳያስነሳ አይቀርም ። ትርፉ ትዝብት እንጂ ስለ እውነት እግዚአብሔር ለቤተክርስቲያንም ሆነ ለሀገሬ መዳንን ከሌላ ሥፍራም ቢሆን ማምጣቱ እንደሁ አይቀርም ። መርዶክዮስም እንዲህ ነበር ያለው ።
" መርዶክዮስም አክራትዮስን። ሂድና ለአስቴር እንዲህ በላት አለው። አንቺ። በንጉሥ ቤት ስለ ሆንሁ ከአይሁድ ሁሉ ይልቅ እድናለሁ ብለሽ በልብሽ አታስቢ።
.....በዚህ ጊዜ ቸል ብትዪ ዕረፍትና መዳን ለአይሁድ ከሌላ ስፍራ ይሆንላቸዋል፥ አንቺና የአባትሽ ቤት ግን ትጠፋላችሁ፤ ደግሞስ ወደ መንግሥት የመጣሽው እንደዚህ ላለው ጊዜ እንደ ሆነ ማን ያውቃል? "
እግዚአብሔር ይመስገን ቁጥራቸው ጥቂት ሆነብኝ እንጂ ከእኔ ጋር የሚታገሉ የትግራይ ልጆች የሉም ማለቴ ግን አይደለም ። በሽሬ ፣ በአክሱም ሆነው ፣ በመቀሌና በአዲግራትም ተቀምጠው አይዞህ ዘመዴ ፣ ከአንተው ጋር ነን የሚሉ ወንድሞች አሉ ። እግዚአብሔር እናንተን አያሳጣን ፣ ሺህ ያድርጋችሁ ።
ለዛሬ አበቃሁ.! ።
"ግን እላለሁ !!! እምዬ ኦርቶዶክስ አንቺ እናትዓለም ፤ የእነ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ፣ የእነ ቅዱስ አትናቴዎስ እና ቅዱስ ቄርሎስ የእነ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፣ የእነ ቅድስት አርሴማ ፣ የእነ አቡነ ተክለሃይማኖት ፣ የእነ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ፣ የአባ ሳሙኤል ዘዋልድባና የአቡነ አረጋዊ ሃይማኖታቸው የሆንሽ ንጽህት ተዋሕዶ ሃይማኖቴ ሆይ ! ብረሳሽና ብከዳሽ ቀኜም ትርሳኝ፣ ትክዳኝም ። ባላስብሽና ባልሞትልሽ ምላሴ ከጉሮሮዬ ይጣበቅ ። ሳለጎበድድና ሳለከዳሽ እንድኖርም አምላክሽ ይርዳኝ ። ይህን ባለደርግና ሳልጮህልሽ ዝም ብዬ ብሞት ፤ ስሜ ከህይወት መጽሐፍ ይደምሰስ ።
"ጌታ ሆይ! ከዚህ በፊት በሆነው ፤ አሁንም እየሆነ ባለው ነገር እና ወደፊትም በሚሆነው ሁሉ ፤ ክብሩን አንተ ውሰድ ።" አሜን. !
"ድንግል ሆይ እናቴ ! አዛኝቱ ዛሬም እንደትናንቱ ቅደሚ ከፊት ከኋላዬ "
ይህንንም ራሴው በእጄ ጻፍኩት ። +4915217428134 ደግሞ የቫይበር ፣ የኢሞና የኋትስአፕ መልእክቶችን የምቀበልበት የእጅ ስልኬ ነው ።
ሻሎም.! ሰላም.!
ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
ግንቦት 28/2009 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ ።

አዝማሪ ትዝታው የራሱንና የቤተሰቡን የአንገት ማዕተብ ከበጠሰ ቆየ ።

ግሪሳ ትዝታው ( ሉንጎ )  መቅሰፍት ሊወርድበት  ነው ★ ★ ★ ✔  Share ~ Comment ~ Like ~ Tag ★ አዝማሪ ትዝታው የራሱንና የቤተሰቡን የአንገት ማዕተብ ከበጠሰ ቆየ ። ★በኮሎራዶ.! ...