ግሪሳ ትዝታው ( ሉንጎ ) መቅሰፍት ሊወርድበት ነው

★ ★ ★

★ አዝማሪ ትዝታው የራሱንና የቤተሰቡን የአንገት ማዕተብ ከበጠሰ ቆየ ።
★በኮሎራዶ.! አለ ነገር.! የሚሰማ.! የሚነገርም አለ ነገር ።

★ እንዲህ ያለውን ጦማር
✔Share ~ Share
✔ ማድረግ በፀረ ተሃድሶው ትግል እጅግ ወሳኝ ነገር ነው ። መረጃው ብዙ ሰው እጅ ገብቶ የመወያያ አጀንዳ ይሆናል ፣ ብዙዎችንም ያነቃል ፣ ጥንቃቄም እንዲወስዱ ያደርጋልና ነው። Comment መስጠትም ሌላው ወሳኝ ነገር ነው ። ደግሞ አስተያየት ስትሰጡ አትልመጥመጡ ፣ አትቅለስለሱ ፣ ወንድ ወንድ የሚሸት አስተያየት ስጡ ።


★ ሚሊዮኖች የእኔን ፔጅ ያነባሉ ፤ በተለይ አገልጋዮችና ወግ አጥባቂ ምዕመናንን እንደ ጉድ ያነቡኛል ። ነገር ግን ጦማሩን ሼር አያደርጉም ፣ ኮመንት አይሰጡም ። ምክንያት ሲባሉ " ዘመዴ በጽሑፎቹ ውስጥ ግሪሳ ፣ በጥራቃ የሚል ቃል ስለሚጠቀም አናደርገውም ይላሉ ። እነዚህ አስመሳዮች ናቸው ። እርቃኗን የቆመች ሴት ፎቶ ሼር እያደረጉ የእኔ ግሪሳ የሚል ጽሑፍ ዘገነናቸው ። እነዚህ የፌስቡክ ላይ ክርስቲያኖች ፣ ናቸው ። የፌስ ቡክ ላይ ጧሚ ፣ ጸሎተኛና ትሁቶች ። እናም እንኳን ሼር አለማድረግ አይደለም ለምን ሳያነቡት አይቀሩም ። ምድረ በጥራቃ ሁላ.!!!
አሁን ወደ ግሪሳው አዝማሪ ትዝታው( ሉንጎ ) ዜና እናልፋለን ። መልካም ቆይታ.! ።
......በመጀመሪያው የ1997 ዓም ምርጫ ወቅት የፖለቲካው ትኩሳት በጋመበት ሰዓት አዲስ መንግሥት ይመጣል በሚል ተስፋ በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ እያለ እሱን ራሱን ሉንጎን ጨምሮ 11 ልጆች በመሆን ኢህአዴግን በመቃወም ለቅንጅት ድጋፍ በመስጠት ፤ በድፍረት የወያኔን አገዛዝ በመቃወም ለተባበሩት መንግሥታት ፣ ለአፍሪካ ኅብረት ፣ ለአረብ ሊግ ፣ ለአሜሪካና እንጊሊዝ መንግሥታት ሳይቀር የተቃውሞ ደብዳቤ ካስገቡት ግለሰቦች መካከል የነበረ ግለሰብ ነው ። ትዝታው ( ሉንጎ)
እኔ ራሴን ጨቅጭቀውኝ ድርጅቴ ድረስ በመምጣት " ዘመዴ!! "ኢህአዴግን ተቃውመን መግለጫ የምንሰጥበት ሚዲያ ፈልግልን ባሉኝ መሠረት በወቅቱ ተነባቢ ጋዜጣ የነበረችውን " ነፃነት " የተባለችው ጋዜጣ ላይ መግለጫ እንዲያወጡ ጋዜጠኛ " ደረጀን በመጥራት ኦዳ ራመት በተባለ ሆቴል ውስጥ በግዋሻው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዲሰጥ አስደርጌው ነበረ ። በወቅቱ ከ" ንክር ፋራና ሰገጤ የገጠር ልጅነት በመውጣት በዝግመተ ለውጥ ወደ አራድነት መጠጋት የጀማመሩበት ወቅትም ስለነበር " እርዳን አግዘን " ባሉን ነገር ሁሉ ሳግዛቸው ነበር ።
የቅንጅት አሸናፊነት ሲከሽፍ እነ ትዝታው ሉንጎ ከመንፈሳዊ ኮሌጅ በደብዳቤ ተባረሩ ። ወዲያውም የሚበሉት ሲያጡ በአዋሽ ባንክ አካውንት ከፍተው እርዳታ መለመን ጀመሩ ። የሚገርመው የባንክ አካውንቱ እስከዛሬ አልተዘጋም ። የዚህን ጊዜ ነው ኢህአዴግን መቃወም እንጀራ እንደሚያስገኝ የተረዱት እነ በግዋሻው ወዲያውኑ ከፓስተር መለሰ ወጉ የተገለበጠውን " የመስቀሉ ስር ቁማርተኞች " የምትል አነስተኛ ፓፍሌት መሳይ የመጽሐፍ ስም የተሰጣት ፓፍሌት በማሳተም አገር ምድሩን አንቀጠቀጡት ። መጽሔቷ በበጋሻው ስም ትውጣ እንጂ ትዝታው ሉንጎም የበረሃ ጓዱ ስለነበር ጥቅሙ የጋራቸው ነበር ። በወቅቱ በፓፍሌታ የተናደደው ወያኔ በጋሻውን ይዞ ማእከላዊ አሰረው ።
ያኔ ነው እኔም ጌቱ ከሚባለው የአብ መዝሙር ቤት ባለቤት ጋር በጋሻውን ለመጠየቅ ማእከላዊ ስሄድ የበጋሻውን እናት ለመተዋወቅ የበቃሁት ። የበጌ እናት በንዴት ኒያላ የተባለውን ሲጋራ በላይ በላዩ እያጨሱ " ተው ብዬህ ነበረ ። አልሰማ አልከኝ ፣ ውቃቢዬ አውሊያዬ ነግሮኛል ። እረፍ ብዬህ ነበር እያሉት ሲቆጡት የደረስኩት " የበጌ እናት በለአውሊያ መሆናቸውን እና በቤታቸው ለብዙዎች የሚፈርዱ በለዛር ሴት መሆናቸውን የዚያን ቀን ነበረ በአይኔ ያየሁት በጆሮዬም የሰማሁት ። አቤት በግዋሻው እንዴት እንደአበደ ። " ማን ጠይቂኝ አለሽ? ፣ ማን ነይ አለሽ? ፣ ሁለተኛ አትምጪብኝ እያለ ሲያለቃቅስ አሳዘነኝ ። እናቱን እንኳ ከአጋንንት አሰራር አውጥቶ ወደ ህይወት መንገድ ያልመለሰ ሰባኪ ያውም ሳይማር መጋቤ ሀዲስ የሚባል ማዕረግ የተሸከመ ፍልጥ እና ዥልጥ ያለ " ሀ " ገደሉ የሆነ ሰው ነው እንግዲህ ሌሎችን አስተምሬ መንግሥተ ሰማያት ካላስገባሁ ሞቼ እገኛለሁ የሚለው በጥራቃ ።
እንግዲህ ከዚህ ከማዕከላዊ እስር በኋላ ነው በግዋሻው ከተቃውሞ ትእቢቱ ተንፍሶ በመውጣት ከመቅስፈት ትዝታው ሎንጎን ጨምሮ ብዙዎቹ የደኢህዴን ኢህአዴግ ደጋፊና አባል ለመሆን የበቁት ። ሉንጎ ከመናፍቁ " አባ " ሰረቀ ጋር በመሆን ከኢህአዴግ የተሰጣቸውን ተልእኮ ለማስፈፀምና ማኅበረ ቅዱሳንን የማፍረስ ፕሮጀክት ከበጋሻው ጋር ሓለፊነት ወስዶ ይንቀሳቀስና እንዲንቀሳቀስ የተደረገ ግለሰብ ነበር ።
የሁሉም መሪና ጠርናፊ ደግሞ በፊት የማኅበረ ቅዱሳን አባል ሆኖ ራሱ ማኅበረ ቅዱሳንን እንዲሰልል ኃላፊነት ወስዶ የነበረውና አሁን በሀገረ አሜሪካ የሚገኘው ቀሲስ ሰሎሞን ሙልጌታ ነበር ። ዱባይ ላይ ቤተክርስቲያን እንዲከፈት ያደረገ ፣ የሚሊንየሙ ጉባኤን ከጀርባ በመሆን ለያሬድ አደመ ትእዛዝ በመስጠት በቤተክርስቲያን ስም ምእመናን ገንዘባቸውን እንዲዘረፉ ያደረገው ግለሰብ ነው ሰሎሞን ማለት ። ይሄው ሰሎሞን ሰሞኑን ዘማሪ ወንደሰን በቀለና ዲን ዳዊትን ይዞ ሲያለቃቅስብኝ መክረሙን አይቻለሁ ሰምቻለሁም ። ወንዴና ዴቭ ፣ አካሉና እስክንድር በጊዜ ሚናችሁን ለዩ ። መረጫጨት ከተጀመረ ለእናንተ ጥሩ አይመጣም ።
በከፍተኛ የስኳር ህመም የሚሰቃየው ግሪሳ ትዝታው (ሉንጎ ) በኢትዮጵያ በተለይ በዲላ ከተማ የማኅበረ ቅዱሳን ቢሮዎችን ለጊዜውም ቢሆን እንዲታሸጉ ያደረገም ግለሰብ ነው ። የድምፅ ቅጂውንም" አርማጌዶን " በተሰኘው ቪሲዲዬ ላይ ተመልከቱት ። እንዲህ እንዲህ እያለ እንደምንም ብሎ በሴት ጀርባ ላይ ተንጠልጥሎ " ገሌ " በመሆን አሜሪካ የገባው ሉንጎ ፤ አሜሪካ እንደገባ ወዲያውኑ የወያኔነት ካባውን አውልቆ የስደተኛውን ሲኖዶስ በመቀላቀል ዋነኛ የወያኔ ተቃዋሚ ሆኖ አረፈው ። በኢትዮጵያ ሳለ እኔን ለመደበቅ ሲል የሟቹን ፓትሪያርክ የአብነ ጳውሎስን ኃውልት አሰሪ ኮሚቴ የነበረ ሰው አሁን ደግሞ በአሜሪካ ከአቡነ መርቆሬዎስ ሥር ተለጥፎ ያሽካካልኛል ። ምደረ አረፊ ፖለቲከኛ ነኝ የሚለውን የድሮ አራዳ ሁሉ ይጫወትበታል ።
አሜሪካን ከገባ በኋላ የውጪውን ሲኖዶስ እንደ መደበቂያ ሽፋን በመጠቀም ያለፉትን ጥቂት ዓመታት በዴንቨር ኮሎራዶ ደግማዊት ግሸን ማርያም ቤተክርስቲያን ውስጥ መሽጎ የስህተት መርዙን በተናጥል በየግለሰቦች ላይ በመዝራት ፤ እሱ ከመምጣቱ በፊት ፍቅር በፍቅር የነበሩትን ግለሰቦች ሆድና ጀርባ አድርጓቸው ቆይቷል ። በተለይ አሁን ቤተክርስቲያኒቱን የሚያስተዳድሩት አባት ጥበብ በተሞላበት አካሄድ ውልፍት እንዳይል ሰቅዘው በመያዝ አላላውስ ብለው በጥበብ ያዙት እንጂ ልጁ ዋና አላማው የቤተክርስቲያኒቱን አስተዳደር በመያዝ የግሪሳዎቹ መፈንጫ ለማድርግ ነበር ዋና ፍላጎቱ ። በዚህ በኩል ቦርዱ ፊት በለመስጠት ያደረገው በጎ ነገር ያስመሰግነዋል ።
የቤተክርስቲያኒቱ ቦርድ በመጀመሪያዎቹ ዓመታት ለግሪሳው ጥብቅና በመቆም ይከራከርለት የነበረ ብቻ ሳይሆን ከ 3500 ዶላር በላይ የደምወዝ እየከፈለው አንደላቅቆ ያኖረው የነበረ ቢሆንም ዘንድሮ ግን አሁን የአሜሪካው ስደተኛው ሲኖዶስ በደብሯ ላይ ስብሰባ ማድረጉን ተከትሎ አጋጣሚውን በመጠቀም የምንፍቅና ሸቀጡን ለማራገፍ በመቋመጥ በይድረስ ይድረስ የተዘጋጀና ከየትኛውም የቤተክርስቲያን ዓውደምህረት ሳትወገዝ የተወገደችውን በመናፍቋ ፓስተር " ዘርፌ " አጃቢነት የቀረበ ቀረርቶ በተከበረችው ደብር ስም ለመሸጥና ዶላር ለማጋበስ ቋምጦ የነበረውን ሉንጎ ያደረገውን አሳፋሪና ፍፁም ስግብግብነት የተመላበት ሙከራ በመመልከት ይህን ሸቃጭ ነጋዴ " ቀረርቶህ በደብራችን ውስጥ አይሸጥም " በማለት ቦርዱ ወሽመጡን በጥሶ ጥሎለታል ።
የቦርዱ ውሳኔ የበጋ መብረቅ ያህል የሆነበትና የደነገጠው ሉንጎም በሁኔታው "ፍዝዝ ፣ ቅዝዝ " ከማለትና ጨጓራዬን አመመኝ ብሎ ከመተኛት ውጪ ምንም ምላሽ ያልነበረው ሲሆን የትዝታው ባለቤት ግን ጨርቋን ጥላ ፤ አቅሏንም ስታ ማበድ እስኪቀራት ድረስ ያዙኝ ልቀቁኝ ፣ ምን ሲደረግ ነው የአዝማሪው ባሌ ቀረርቶ የማይሸጠው በማለት አዋራ ስታስነሳ እንደነበር ታይታለች ። ከምር በእጄ የገባውን ቪድዮ ሳይ አሳዘነችኝ ። ለቅዱሳን ክብር አይገባም በማለት ማኅተባቸውን የበጠሱት ባልና ሚስቱ ቤተክርስቲያንን የሚፈልጓት " ለሸቀጥ ማራገፊያነት " ነውም ተብሏል ።
አሁን ከትዝታው ጎን የቆሙት ጥቂት ቤቢ ሲተሮችና የቤተክርስቲያኒቱ ቦርድ ውስጥ ካሉት አባላት መካከል አንዲት ሴት ስትሆን ፤ በተለይ ሴትየዋ በቦርድ ደረጃ የተነጋገሩትን ይዛ በመውጣት ለሉንጎ በመንገር እሱም አድማ የሚመቱ ቤቢ ሲተሮችን በማዘጋጀት እስከአሁን ሲንቀሳቀስ ቆይቷል ። አሁን ግን በትዜ ላይ ጀንበር የጠለቀች ይመስላል ። የሚገርመው ነገር ደግሞ ሴትየዋ ይህን አይነት ድጋፍ ስትሰጠው ባለቤቷ አቶ ታረቀኝ ደግሞ ከቅድስት ቤተክርስቲያን ጎን የቆመ መሆኑ ነው ።
የሚገርመው ነገር የአሜሪካው ሲኖዶስም በዘንድሮው ስብሰባው በማጠቃለያው ላይ በሰጠው ውሳኔ በ6 ተኛው ተራ ቁጥር ላይ " ተሃድሶ የሚባል አዲስ ሃይማኖት መጥቷልና " ተጠንቀቁ በማለት በድፍረት ሲናገር ተደምጧል ። ተሃድሶ የሚባል የለም ባዩን ግሪሳ ትዝታውን በተቀመጠበት ውኃ የቸለሰበት ውሳኔ ሲሆን ፣ በአንፃሩ ደግሞ ተሃድሶ ያስፈልጋል ባዮቹን አባ ወልደትንሳኤንና አባ ገብረሥላሴን ጳጳስ አድርጎ በመሾም ፣ እነ ልኡለቃልን ፣ እነሽታ ቡዝዬን ፣ እነ እንዳልካቸው ዳኘውንና ፣ እነ ፓስተር መላኩን አዝሎ እየዞረ ስለ ተሃድሶ ቢያወራ ሰሚ የሚያገኝም አይመስልም ። እርግጥ ነው ፤ ይፋ አይውጣ እንጂ በዘንድሮው ስብሰባቸው " ለአባ ወልደትንሣኤ አያልነህ " ከባድ የተባለ ማስጠንቀቂያ እንደተሰጣቸው ውስጥ ውስጡን ይወራል ። ለዚህም ነው በዴንቨሩ ስብሰባ አባ ወልዴ ድምጻቸውም መልካቸውም ድራሹ የጠፋው የሚሉ ሰዎች የበዙት ።
አሁን ለምድረ ተሃድሶ ሁላ አሜሪካ ውስጥ ይሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ብቻ የትም ይሁን የት በሁሉም ቦታዎች መንገዶች ሁሉ ዝግ ሆነውባቸዋል ። የሚያስተምሩበት መድረክ ተነጠቀዋል ። እሰከ ዛሬ ያለ ከልካይ ሸቀጣቸውን ያራግፉበት የነበረው ዓውደምህረት ዝግ ሆኗል ። የትዝታው ዘፈን በራሱ በፕሮቴስታንቶችና የንግድ ድርጅቶች ውስጥ በይፋ መሸጥ ተጀምሯል ። ዴንቨር ኮሎራዶ የፕሮቴስታንቶች ጸጉር ቤት ውስጥ ለሽያጭ መቅረቡ ታይቷል ። እናም አሁን ሁሉም ባንኗል ። ያልባነነው ደብሯ የቦርድ አስተዳደር ብቻ ነው ።
ወይዘሮ ስፍነ የሰንበት ትምህርት ቤቱ ሊቀንበር ናት ። የትዝታውም ድብን ያለች ቲፎዞም ነበረች ። ኋላ ላይ ግን እየቆየች ስትመጣ ነገር ዓለሙ ሁሉ ተገለጠላት በተለይ የእመቤታችንን መዝሙር እንዲዘምር ፤ ልጆቹንም እንዲያስጠና የምትመክረውን ምክር ባለመስማት ለእመቤታችን አልዘምርም ካላት ጊዜ ጀምሮ በአንድ ጊዜ እሳትና ጭድ ሆነው ከርመዋል ።
አሁን ያበጠ ነገር የሚፈነዳ ያለ ይመስላል ። በውስጥ መስመር ከደብሯ እንደሚደርሱኝ መረጃዎች ከሆነ የደብሯ የበላይ ጠባቂ አቡነ ናትናኤል የተባሉት አባት ሉንጎን ጉድ ሳርተው መላው ዓለም ላይ የሚገኙ ኦርቶዶክሳውያንን ጮቤ ያስረግጣሉ እየተባለም ነው ። ሉንጎ ሉቡ ተራራ ነው ። ከደብሯ ቢባረር ጥቂት የደቡብ ልጆችና ቤቢ ሲተሮች ቢከተሉት እንጂ እሱን ተከትሎ የሚወጣ አንድም ሰው አይኖርም ።
የመረጃ ምንጮቼ እንደሚሰጡኝ መረጃ ከሆነ የቤተክርስቲያኒቱ ሽማግሌዎች እጅግ ጠንካራ ሽማግሌዎች መሆናቸው ይነገርላቸዋል ። በሃይማኖት ቢሉ በሀገር ፍቅር የሚታሙ አይደሉምም ይባላል ። እነ አቶ ጥላሁን ፣ ዲን ዮሴፍ ፣ አቶ ታሪኩ ፣ አቶ ሞላ ፣ አቶ ባዬ ፣ አቶ ናርዶስ ፣ አቶ ዳዊት ፣ አቶ ለገሰ ፣ ወጣት ነብዩ ፣ አቶ ለይኩን ፣ አቶ ኤፍሬም እና ዶር አሰፋን ፣ የያዘው ቦርድ እስከዛሬ ክፉ ደጉን አብረው ያሳለፉትን ምእመናን ብሶትና ሮሮ ሳይሰማ ጆሮውን ደፍኖ ለአንድ ተራ መናፍቅና ፀረ ማርያም ወንበዴ ጥብቅና በመቆሙ ብዙዎች ሲያዝኑ ኖረዋል ። አሁን ግን አለ ነገር እየተባለ ነው ።??? አለ ነገር.??
በመጨረሻም አዝማሪ " ትዝታው" ከዚህ በፊት እኮ ለእመቤታችን ዘምሯል ፤ እንዲያው ምን ነክቶት ነው ብለው ለሚሟገቱ " ምስኪኖች " አዎ ዘምሯል ። ምልጃዋንም አሳምሮ ዘምሯል ይሄ ሁሉ እውነት ። ነገር ግን አሁን አዝማሪው የእመቤታችንን ስም ማንሳት እንደነውር መቁጠር ከጀመረ ቆየ ። በፊት ስለ እመቤታችን ዘመረ ከተባለው ቀረርቶ መካከልም እስቴ አንዱን ጋብዣችሁ እንሰነባበት። "
ወደስኒ ካልሽኝማ " ።
★★ ★
ወድሰኒ ከልሽኝማ
አመስግነኝ ካልሽኝማ
አመስግነኝ ካልሽኝማ
ይልና አዝማሪ ትዝታው ፤ እንዲህ ይደረግ ፤ ምስጋና አምሮኛል ካልሽኝ ፤ መመስገኑንም ከፈለግሽ ፣ እናም ካስቸገርሽኝ ፤ የግድም ብለሽ ወጥረሽ ከያዝሽኝ ፣ ጭቅጭቅም ካደረግሽኝ እንግዲያው እኔ እንዳመሰግንሽ በቅድሚያ ማሟላት ያለብሽን ልንገርሽ ይላታል ደፋሩ ሉንጎ እመቤታችንን ። ለቅዱስ ኤፍሬም ተደረገ የተባለው እውነት ከሆነና ፤ አሁንም ልክ እንደ ቅዱስ ኤፍሬም እኔም እንዳመሰግንሽ ከፈለግሽ ፦
፩ኛ፤ በደመና ውረጂና
፪ኛ፤ የእሳት አትሮንስ ይዘርጋና
፫ኛ፣ የወርቅ ምንጣፍ ይዘርጋና
፬ኛ፣ ላመስግንሽ እንደገና ፤
ያለበለዚያ በዚህ ስምምነታችም መሰረት ለቅዱስ ኤፍሬም አደረግሽ የተባለው ነገር የማይደረግ ከሆነ ስለአንቺ የመዘመር ግዴታ የለብኝም ነው " ፈረንሳይኛው " ።
እናንት የእናት ጡት ነካሾች የገባችሁበት ብትገቡ አልፋታችሁም ። አይደለም አሜሪካ ጠፈር ላይ ብትወጡ እንዲሁ በዋዛ አልለቃችሁም ። ንስሃ ትገቡ እንደሁ ብዬ በብርቱ ጠበቅኳችሁ እናንተ ግን ባሰባችሁ እንጂ የሰናፍጭ ቅንጣት ታህል የመጸጸት ነገር አላሳያችሁም ። ስለዚህ አልፋታችሁም ። ምን ያህል በእናንተ ላይ የእናንተን የውስጥ አንጀት ጉበት ገልብጬ ለህዝቡ ለማሳየት ዋጋ እንደከፈልኩ ልባችሁ ያውቀዋል ።
★ ሀገሬን ★ ቤተሰቤን ★ ልጆቼንና ጓደኞቼን አጥቼማ ያለውጤት ዝም ብዬ የምቀመጥ አይምሰላችሁ ። ወዳጄ ትእዛዙ ከላይ ነውና አንላቀቃትም .!! ። የማንንም ድጋፍ አልሻም ። የሲኖዶስ ውግዘትም አልጠብቅም ፤ ረድኤተ እግዚአብሔርን አጋዥ አድርጌ፣ የብርሃን እናት ወላዲተአምላክን ይዤ ፣ በቅዱሳኑ ጸሎትና ምልጃ እየታገዝኩ አፈር ከድሜ ማስጋጥ እንደሁ አያቅተኝም ። ሲያዩዋችሁ ለተመልካች ጎልያድ ብትመስሉም እናንተን አጋድሞ ከ " ተዋሕዶ " ትከሻ ላይ ለማራገፍ የዳዊት ጠጠርና ወንጭፉ በቂ ነው ። አለቀ ። አራት ነጥብ ።
ማሳሰቢያ.! በውጪው ሲኖዶስ ሥር ለምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች በሙሉ ። ወያኔም መውደቁ ፣ አንድ ቀን ታሪክ መሆኑ አይቀርም ። በወያኔ አኩርፋችሁ እንጂ እምነታችሁ ያው የጥንቱ የጥዋቱ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ መሆኗ ይታወቃል ። ነገ እግዚአብሔር ሲፈቅድ ፤ በቃችሁ ሲለንም አንድ መሆናችን አይቀርም ። ጊዜው ሩቅ እንዳይሆን መጸለይም አለብን ። እናም ገና ለገና እላይ ያሉት የሃይማኖት አባቶች ተጣልተዋል ፣ የሚታረቁም አይመስልም በሚል ሰበብ የማንም ልቅምቃሚ መናፍቅ መጫወቻና መጠራቀሚያ መሆን የለባችሁም ። ተአምረ ማሪያም የማያነቡ ፣ ሴቶችን ታቦት ማየት ትፈልጋላችሁ ወይ እያሉ በድፍረት ከመንበሩ ላይ ወስደው ለማሳየት የሚሞክሩ ፣ በሥጋወ ደሙ የሚያላግጡ ፣ ሴቶችን ታቦቱ ያለበት መንበሩ ድረስ አስገብተው ጽዳት እንዲያፀዱ የሚያደርጉ ግልፅ መናፍቅ የሆኑ ግለሰቦችን ልትቃወሙ ይገባል ። የምንለያይባቸው ብዙ ሀገራዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ቢኖሩም በእምነታችን ግን አንድ ነን ። እናም በአንድነት እንታገላቸው ።
እነዚህ ሰዎች በጣም ብዙ አይደሉም ፣ ነገሩ ነጭ ልብስ ላይ እንዳረፈ ጥቁር ነጥብ ሆነው ጎልተው ይታያሉ እንጂ ብዙ አይደሉም ። ከፈለጋችሁ በፎቶ አሳያችኋለሁ ። ከእነዚህ ሰዎች ራቁ ። በእውነት ራቁ ብያለሁ ። የኢትዮጵያ አምላክ ለእነዚህ አጥፊዎች የእጃቸውን ይሰጣል ፣ እንዲህ አምናለሁ ። እንዲህም እታመናለሁ ። ለዛሬ አበቃሁ ።
በቀጣይ የዘርፌን ወቅታዊ ሁኔታና ያለችበትን አሳዛኝ ህይወት እንመለከታለን ። አከተመ ።
"ግን እላለሁ !!! እምዬ ኦርቶዶክስ አንቺ እናትዓለም ፤ የእነ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ፣ የእነ ቅዱስ አትናቴዎስ እና ቅዱስ ቄርሎስ የእነ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፣ የእነ ቅድስት አርሴማ ፣ የእነ አቡነ ተክለሃይማኖት ፣ የእነ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ፣ የአባ ሳሙኤል ዘዋልድባና የአቡነ አረጋዊ ሃይማኖታቸው የሆንሽ ንጽህት ተዋሕዶ ሃይማኖቴ ሆይ ! ብረሳሽና ብከዳሽ ቀኜም ትርሳኝ፣ ትክዳኝም ። ባላስብሽና ባልሞትልሽ ምላሴ ከጉሮሮዬ ይጣበቅ ። ሳለጎበድድና ሳለከዳሽ እንድኖርም አምላክሽ ይርዳኝ ። ይህን ባለደርግና ሳልጮህልሽ ዝም ብዬ ብሞት ፤ ስሜ ከህይወት መጽሐፍ ይደምሰስ ።
"ጌታ ሆይ! ከዚህ በፊት በሆነው ፤ አሁንም እየሆነ ባለው ነገር እና ወደፊትም በሚሆነው ሁሉ ፤ ክብሩን አንተ ውሰድ ።" አሜን. !
"ድንግል ሆይ እናቴ ! አዛኝቱ ዛሬም እንደትናንቱ ቅደሚ ከፊት ከኋላዬ "
ይህንንም ራሴው በእጄ ጻፍኩት ። +4915217428134 ደግሞ የቫይበር ፣ የኢሞና የኋትስአፕ መልእክቶችን የምቀበልበት የእጅ ስልኬ ነው ።
ሻሎም.! ሰላም.!
ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
ግንቦት 27/2009 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ ።
ግንቦት 27/2009 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ ።
No comments:
Post a Comment