Thursday, 25 May 2017

የመርሕ ጥያቄ ? ? ? በዲን ዳንኤል ክብረት

የመርሕ ጥያቄ
? ? ?
በዲን ዳንኤል ክብረት
★ ★ ★
በዚህ 15 ቀን ብቻ ፔጄን ያዩ የተመለከቱ ሰዎች ቁጥር 9 ሚልየን ሊገባ መሆኑን ፌስቡክ እየነገረኝ ነው ። ታዲያ በዚህ መጠን ሰው ማግኘትና መድረስ ከቻልን የምን EBC. ን መለማመጥ ነው ። ዳይ ወደ ዘመዴ ገጽ መረጃ መላክ ብቻ ነው የሚጠበቅባችሁ ።
Share ~በማድረግ ላላየ እናሳዩ ፤ ላልሰማም እአሰሙ ።
Comment ~በመስጠት በድርጊቱ ላይ ተወያዩ ።
Tag ~ በማድረግ በፉጨት የተሻሉ ሰዎችን እንጥራ ።
እስይ ደስ ሲል ይኸው አሁን በስተመጨረሻም ቢሆን እነ ዳኒም መጡልኝ.! እንዴ ብቻዬን ልፈንዳ እንዴ.!? ሆሆይ.! ደግሞም ባይመጡም ጉዳዬ አልነበረም ። እንደውሻ ለመጮህ ማን ብሎኝ.??? እንደ እብድ ፣ ደግሞም እንደ ውሻ እጮሃለሁ ።
በነገራችን ላይ.! የዛሬን አያድርገውና ደያቆን ዳንኤል ክብረትና ባለቤቱ ወይዘሮ ጽላት ፤ እኔ ቃሊቲ በታሰርኩ ጊዜ ልጆቼን አርብ አርብ ከቤቴ ወስደው ቅዳሜና እሁድ ከልጆቻቸው ጋር አውለው ፣ አጫውተው ፣ እሁድ ማታ ወደ ቤቴ ይመልሱዋቸው ነበር ። ምክንያቱን ባላውቀውም ያ ሁላ ነገር ግን አሁን የለም ። እንዲያም ሆኖም ግን ዳኒ በእኔ ልብ ውስጥ " ልዩ " ስፍራ ነው ያለው ።
የሚገርማችሁ ነገር ዲን ታደሰ ትናንት የግድያ ሙከራ ከተደረገበት በኋላ አርፎ ይቀመጣል ብዬ ስጠብቀው ብሶበት ቁጭ ብሏል " ። ታዴ አረ እንዴት ነው ስለውም ፤ አይደለም በመኪና ከፈለጉ በአውሮፕላን ለምን አይገጩኝም ከእንግዲህ ወዲህ መላቀቅ ብሎ ነገር አይታሰብም ብሎ አስደስቶኛል ። እናም ይኽን የዲን ዳንኤል ክብረትን ከዶክተር አባ ኃይለማርያም ጋር የገጠመውን ሙግትና የሚያቀርበውን ጥያቄ እያነበብን ከቆየን በኋላ ጊዜ ሲገኝ የታዴ አዲሱ ጦማርም ይለቀቅላችኋል ። እናንተ ብቻ ፀባይ አሳምራችሁ በያላችሁበት ቦታ ሆናችሁ ፦
 በፓትርያርክ አቡነ ማትያስ.!
 በአቡነ ቀውስጦስ
 በአቡነ ቄርሎስ
 በአቡነ ገብርኤል
 በአቡነ ቀሌሜንጦስ
በእነ ዚህ አባቶች ጨጓራችሁን እየላጣችሁ ፤ እርር ድብን እያላችሁ ፣ ትንፋሻችሁን ቁርጥ ቁርጥ እያደረጋችሁ ። ጠብቁኝ ። እነዚህ አምስት አባቶች ቅድስት ቤተክርስቲያንን ተማምለው ጉድጓድ ሊከቷት ያሰፈሰፉ አባቶቻችን ናቸው ። እናም አንድ እግራችሁን ከመቃብር አፋፍ ከትታችሁ ሳለ ፤ ቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ ዶር አባ ኃይለማርያምን የመሰለ 666 መልእክተኛ ፤ አባ ተክለሃይማኖትን የመሰለ የመንግሥት ቅጥረኛ ጳጳስ ለማድረግ ያሴሩ ፣ የቅዱስ ሲኖዶሱንና የመንፈስ ቅዱስን ልዕልና የተዳፈሩ አባቶች ናቸው ። ጉዳዩን እስኪያስተካክሉ መቃብር እስክገባ ድረስ በየምክንያቱ እያነሳሁ ስወቅሳቸው ዘላለሜን እኖራለሁ ።
ዲን ዳንኤል ክብረት እስከ አሁን ዝም ጭጭ ትንፍሽም ሳይል ከርሞ አሁን በስተ መጨረሻ ቢሆን ብቅ ያለ ወንድማችን ነው ። ቢሆንም አልረፈደም ። ደግሞም ከመቅረት ይሻላል ። ልክ እንደ ዲን ዳንኤል ሁሉ አሁንም ቢሆን ዝም ጭጭ ያሉ የሰላም ጊዜ ሐዋርያዎች ሞልተዋል። ዘላለም ወንድሙ የተባለ በሰላሙ ጊዜ በየአውደ ምህረቱ ምስኪን ካህናትን እየዘረጠጠ " ቄሶቹን ልክ ልካ ቸውን ነገራቸው " እየተባለ በጴንጤዎቹ ጭምር ተወዳጅ ለመሆን የበቃና አሁን ቀጭን ኢንቬስተር የሆነው አፈ ጮሌ ሰባኪ ፤ በዚህ ሰዓት ሰማይ ይውጣ ምድር የሚታወቅ ነገር የለም ። እኔ ግን እመጣበታለሁ ።
ዶር ዘበነ የተባለው ወንድማችን ፣ በሰላሙ ጊዜ ከማይመለከታቸው ጴንጤዎች ጋር በመሟገት ፤ ያንንም ሙግት ሲዲ ቪሲዲ እያደረገ መልሶ ሸቀጡን ምእመናን ላይ ሲያራግፍ የኖረ ነጋዴ አሁን ዶርበሆንኩ ካለ በኋላ የት እንደደረሰ መድኃኔዓለም ይወቅ ።
ትንሽ ውር ውር ይል የነበረው መምህር ምህረተ አብ አሰፋም አሁን ድምፁን አጥፍቷል ። መምህር አስቻለው ከበደም ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ከገባ በኋላ ጎመን በጤና ያለ ይመስላል ።
መር ጳውሎስ መልክዓሥላሴ ፣ ዲን ተስፋዬ ሞሲሳ ፣ ዲን ደንኤል ግርማ ፣ ቀሲስ ሱራፌል ወንድሙ ፣ መ/ር በላይ ወርቁ ፣ ዲን ታዲዮስ ግርማ ፣ ቀሲስ ያሬድ ገብረመድኅን ፣ ቀሲስ ደጀኔ ሽፈራው ፣ ቀሲስ ብርሃኑ ጎበና ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ ፣ ዲያቆን ሔኖክ ኃይሌ ፣ ዲን ምትኩ አበራ ፣ መጋቤ ሀዲስ ሮዳስ ፣ መጋቤ እሸቱ አለማየሁ ። ለዛሬ ያልሆናችሁ ለመቼ ልትሆኑ ነው ?? ። የማንን ጎፈሬ እያበጠራችሁ ይሆን ። አንተ ቀሲስ ተስፋዬ መቆያስ ትግሉን ተቀላቅያለሁ ካልክ በኋላ ምነው የበላህ ጅብ አልጮህ አለ.?? አቡኑ ማሞ የተባልክ ሰባኪስ ዝም ብለህ ፊልም እየሠራህ ብቻ መሸቀል ነው እንዴ ሥራህ.?? ተናገር እንጂ.?? አንተ የማለዳ ኮበብ የጥንት የጥዋቱ የወንጌል አርበኛ መምህር ተስፉ ግርማ (አንድምታ) የትደረስክ ። ሊቀሊቃውንት ስምዓኮነ በእውኑ በሀገር ውስጥ አለህን.!??
እመኑኝ ቅድስት ቤተክርስቲያን ምንም አትሆንም ። በመጽሐፍ ቅዱስ መጽሐፈ አስቴር ላይ መርዶክዮስ አክራትዮስን ወደ አስቴር ሲልከው ያለውን ነገር ላስታውሳችሁ።
" በዚህ ጊዜ ቸል ብትዪ ዕረፍትና መዳን ለአይሁድ ከሌላ ስፍራ ይሆንላቸዋል፥ አንቺና የአባትሽ ቤት ግን ትጠፋላችሁ፤ ደግሞስ ወደ መንግሥት የመጣሽው እንደዚህ ላለው ጊዜ እንደ ሆነ ማን ያውቃል? " አስ 4 ፣14
ዳታንና አቤሮን ሙሴና አሮንን ከመቅደሱ አስወጥተው በሌላቸው ስልጣን ቤተመቅደስ አጥነው የርኩሰት ሥራ ፣ የድፍረት ሥራ በፈጸሙ ጊዜ ምድር ተከፍታ እንደዋጠቻቸው ዘኁል 16 ማንበብ ይቻላል ። ዮዲት ጉዲት 40 ዓመት ፣ ግራኝ አህመድ 15 ዓመት ኢትዮጵያንም ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ለማውደም ያልፈነቀሉት ተራራ አልነበረም ። በሰይፍ ልጆቿን ፣ በእሳት ቅርሶቿን ለመውደም ሌት ተቀን ባዘኑ ። እነ ሱ ጠፉ የለምም ፣ ቤተክርስቲያን ግን በክርስቶስ ደም ላይ የተመሠረተች ናትና ይኸው አለች ፣ ወዲፊትም መስሯቿ ክርስቶስ ኢየሱስ በክብር እስኪወስዳት ድረስ ትኖራለች ።
ግን ትዝብት ነው ትርፉ ። ሁላችንም የመናጢ ደሃ ልጆች ነበርን ። ይሄን ጉዳይ ሰይጣንም እግዚአብሔርም እኛም እናውቀዋለን ። አንቱ የተሰኛችሁትም በዚህች ቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ ታይታችሁ ነው ። እናም የእንጀራ ቤታችሁ የሆነችው ፣ የክብር አዳራሻችሁም የሆነቻችሁ ፣ ግርማ ሞገሳችሁ የሆነች እናት ቤተክርስቲያን በዚህ መጠን ስትወጋ ጮጋ ማለታችሁ በእውነት ዝምታችሁ ያስፈራል ። ደግሞ ተወቀስን ብላችሁ ቡራ ከረዩ በሉ አሏችሁ ። ማንም አይሰማችሁም ። ደግሞስ እኔ ታናሽ ወንድማችሁ ያልወቀስኳችሁ ማን እንዲወቅሳችሁ ፈለጋችሁ ። ማንስ ይውቀሳችሁ ። በጭባጫ ሁላ.! በሉ አትንበጫበጩ ። ቱ እውነቴን ነው እናንተ ከአሰግድ ታንሳላችሁ እንዴ .?? ተብታባው ከፍያለው ቱፋ እንዲህ በነጻነት ሲፏልል እያያችሁ ከእሱ ታንሳላችሁ በማርያም.??? ሰው እሳት የሚተፋ ብእርና አንደበት ይዞ እንዴት ይፈራል ። በእውነት ያሳፍራል ። ለማንኛውም እንጠብቃችኋለን ።
አሁን ወደ ዳኒ ጦማር ልውሰዳችሁ.???

......ሰሞኑን ዶክተር አባ ኃይለ ማርያም ኦርቶዶክሳውያን ካልሆኑ አካላት ጋር ያከናወኑትን ‹የጠበልና እምነት› ጉዳይ በተመለከተ አያሌ ጥያቄዎች ሲነሡ ነበር፡፡ ነገሩን ከየምንጮቹ ብሰማቸውም በቅዱስ ጳውሎስ ዘመን የነበረው የቂሣርያው ገዥ ፊስጦስ ‹ተከሳሹ በከሳሾቹ ፊት ለፊት ሳይቆም፣ ለተከሰሰበትም መልስ ይሰጥ ዘንድ ፈንታ ሳያገኝ ማንንም ቢሆን አሳልፎ መስጥ የሮማውያን ሥርዓት አይደለም› (የሓዋ.25፣16) ብሎ የተናገረውን መሠረት በማድረግ አባ ኃይለ ማርያም ለጉዳዩ የሚሰጡትን መልስና ማብራሪያ ጠብቄ ነበር፡፡ መልስና ማብራሪያውንም ሰጡ፡፡
አባ የድርጊቱን መከናወን አምነው የክንውኑን ዓይነት ከተወራው የተለየ መሆኑን አብራሩልን፡፡
መልሳቸውን ስናጠቃልለው፡-
1. መርሐ ግብሩ ‹ውኃ ለሁሉም› በሚል መርሕ እንደተዘጋጀ
2. ፓትርያርኩና ሊቃነ ጳጳሳት እንደተገኙበት
3. ተበጥብጦ ከመጣው ውኃና እምነት ጠቅሰው በተሳታፊዎቹ ግንባር ላይ ምልክት አንዳደረጉ
4. ሰውዬው ጣቱን አስጠጋ እንጂ አንዳልቀባቸው
መርሐ ግብሩ ‹ውኃ ለሁሉም በፍትሐዊነት እንዲዳረስ› ከሆነ እንዴት ነው እምነትና ውኃ በመበጥበጥ ውኃ ለሁሉም ሊዳረስ የሚችለው፡፡ ‹ውኃ ለሁሉም› የሚለው ጉዳይ የዐውደ ጥናት፣ የምክክርና ምናልባትም የጸሎት ርእስ ሊሆን ይችላል እንጂ እምነትን በውኃ በጥብጦ በመቀባት ‹ውኃ ለሁሉም› እንዴት ለማዳረስ ይቻላል? እምነት በውኃ በጥብጦ መቀባት ለፈውስ ያገለግላል እንጂ እንዴት ከውኃ ፍትሐዊ አጠቃቀም ጋር ተገናኘ? ደግሞስ እኛ ከሌሎች እምነቶች ጋር አንድነታችንን ማምጣት ያለብን በክርስቶስ እንጂ እምነት በውኃ በመበጥበጥ ነው እንዴ?
አባ ኃይለ ማርያም በሰውዬው (የሌላ አምነት መሪ መሆኑ ከፎቶውና ከመረጃው ይታወቃል) ግንባር ላይ ሲቀቡት ምን እንዲያደርግ አስበው ነው? እንዲፈወስ የቀረበ በሽተኛ ነው? ለበረከት የመጣ ደጅ ጠኚ ነው? እንዴትስ ነው የተበጠበጠው እምነት ከ‹ ውኃ ለሁሉም› አስተሳሰብ ጋር የሚሄደው?
ሌላው አስገራሚ ነገር ደግሞ ‹ሰውዬው ጣቱን አስጠጋ እንጂ አልቀባኝም› ብለዋል፡፡ ፎቶዎቹ ሁሉ የሚያሳዩት ግን ሲቀባዎት ነው፡፡ ደግሞስ ሰውዬው ለመቀባት ካላሰበ እጁን ለምን ወደ እርስዎ ያስጠጋል? ሊባርክዎ ነው? አስቀድማችሁ የተስማማችሁበት ሥነ ሥርዓት ይህንን የማይፈቅድ ከሆነስ እንዴት እጁን ወደ እርስዎ አስጠጋ? ‹እጁን አስጠግቶ ነበር› ካሉን ደግሞ ከተበጠበጠው እምነት እንደ እርስዎ ጠቅሶ ነበር ማለትዎ ነው? ለመሆኑ ኦርቶዶክሳዊ ክህነት የሌለው ሰው ከእምነት ጠቅሶ ሌላውን ሰው መቀባት፣ ያውም ቆሞሱን ይችላልን?
ሥነ ሥርዓቱ ሲከናወን ፓትርያርኩና ሊቃነ ጳጳሳቱ እንደነበሩ አባም ነግረውናል፣ ፎቶውም አሳይቶናል፡፡ ምን ወስነው? ምን ሊያደርጉ ሄዱ? ውኃ ለሁሉ እንዲዳረስ ሊጸልዩ ወይስ ውኃ ለሁሉ እንዲዳረስ እምነት በውኃ ሊበጠብጡ? ለመሆኑ ይህንን እንዲያደርጉ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን ይፈቅድላቸዋል? ወይስ ሥልጣን ከቀኖና ስለሚበልጥ?
አባን ለዚህ ሁሉ ነገር የዳረጋቸው በቤተ ክርስቲያኒቱ ውስጥ መርሕ እየተጣሰ ስለመጣ ነው፡፡ ሁለት መሠረታዊ ጥያቄዎችን እናንሳ፡-
ቤተ ክርስቲያናችን ኢኩሜኒካል ግንኙነትን የምትመራበት ፖሊሲና ደንብ አላት?
ቤተ ክርስቲያናችን ኢኩሜኒካል ግንኙነቶችን የምታከናውንበት ተቋምስ አላት?
የሁለቱም መልስ የላትም የሚል ነው፡፡ በሌሎች እኅት አብያተ ክርስቲያናት የኢኩሜኒካል ግንኙነትን የተመለከተ ፖሊሲና ደንብ ሲኖዶሱ ያጸድቃል፡፡ ከነማን ጋር ምን ዓይነት ውይይት ይደረጋል፣ ምን ዓይነት ውይይቶች በምን ደረጃ (በሊቃውንት፣ በጳጳሳት) ይደረጋሉ፣ ስምምነቶች እንዴት ይጸድቃሉ፣ የጸደቁት እንዴት ለሕዝብ ይገለጣሉ፣ የጸደቁትን እንዴት መተግበርና መከታተል ይቻላል፣ ስምምነት እስኪደረስ ድረስ ከሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ጋር ምን ዓይነት ግንኙነቶች ይኖሩናል? በምን በምን እንተባበራለን? በየደረጃው ያሉ አካላት (ጳጳሳት፣ ካህናት፣ ዲያቆናትና ምእመናን) ያላቸው ድርሻ ምንድን ነው፣ የሚሉትን የሚወስን የፖሊሲ መዝገብ አላቸው፡፡ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ግን ይህ ፖሊሲ የላትም፡፡ ፖሊሲውንም መሠረት አድርጋ የምትመራበትን ሕግ አላጸደቀችም፡፡ ስብሰባ ስትጠራ መሄድ ብቻ ነው፡፡
በሌላ በኩልም የኢኩሜኒካል ግንኙነትን የሚያካሂድ፣ ባለሞያዎችን የሚሰባስብ፣ መረጃዎችን የሚመዘግብ፣ በዓለም ላይ የሚደረጉ የኢኩሜኒካል ግንኙነቶችን የሚከታተል፣ ግንኙነቶቹን በፖሊሲውና በደንቡ መሠረት የሚመራ፣ ስሕተቶች ሲፈጠሩም የሚያርም ተቋምም የለም፡፡ ያለው የውጭ ግንኙነት መምሪያ ነው፡፡ እርሱ ደግሞ ብዙ ጊዜ እንግሊዝኛ ይችላሉ ተብሎ ስለሚታሰብ አሜሪካ በኖሩ ሰዎች የሚመራ ነው፡፡ የኢኩሜኒካል ግንኙነት ግን የአሜሪካን እንግሊዝኛ በመቻል ብቻ የሚሠራ አልነበረም፡፡ የውጭ ግንኙነት መምሪያው ወደ ውጭ ለሚሄዱ ሰዎች ሂደቶቻቸውን መከታተል፣ ከውጭ አጥቢያዎች ጋር ‹መገናኘት› የሚላኩ ሰዎችን መላክ እንጂ ራሱ እንኳን የሚመራበት የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ ያለው አይመስልም፡፡
ይህ በሆነበት ሁኔታ አባ ኃይለ ማርያም ያንን ነገር ቢያደርጉት የሚገርም አይደለም፡፡ ቅዱስ ሲኖዶሱ፣ በዕለቱ የነበሩት ፓትርያርኩና ሊቃነ ጳጳሳቱ የቤተ ክርስቲያኒቱን መርሕ እየጣሱ ያዘዟቸውን ነው የተገበሩት፡፡ እርሳቸው ቢሆኑም ግን ፖሊሲና ሕግ በሌለበት ይህንን ተግባር ከሚያከናውኑ ‹ዱክትርናቸውን› ተጠቅመው ፖሊሲውና ሕጉ እንዲዘጋጅ ቢያደርጉ ኖሮ ይመሰገኑ ነበር፡፡ ነገ ጳጳስ የሚሆኑትን አባት ማንም እየተነሣ እጁን ወደ ግንባራቸው አይልክም ነበር፡፡ በሃይማኖት መሥመር የበላይ ያመጣውን ሁሉ በእምነት መመርመር ያስፈልጋል፡፡ የበላይ አዞኝ ነው ብሎ ቀኖና መጣስና እምነት ማፋለስ ዋጋ ያስከፍላል፡፡
በጉባኤ ኬልቄዶን የክህደቱን ውሳኔ አልቀበልም ያለው ዲዮስቆሮስ በሮም ቤተ መንግሥት ተጠርቶ ‹ለምን አትቀበልም? ልዮንኮ አለቃህ ነው› ሲባል ‹ልክ ነው ልዮን አለቃዬ ነው፡፡ ነገር ግን ከእምነቱ ሲወጣ አልቀበለውም፡፡ ሳጥናኤልም ለቅዱስ ሚካኤል አለቃው ነበር፤ ከእምነቱ ሲወጣ ግን አልተቀበለውም› ያለውን እዚህ ላይ ማስታወሱ መልካም ነው፡፡ አሁንም ቤተ ክርስቲያናችን ኢኩሜኒዝምን የተመለከተ ፖሊሲና መመሪያ ካላወጣች፣ ጠንካራ ተቋምም ካልመሠረተች ነገ ከዚህ የባሰ ነገር ማየታችን አይቀርም፡፡ ከዚህ ተግባር የተማርነው ግን የቤተ ክርስቲያናችንን ጉዳይ በነቃ ኅሊና መከታተል እንዳለብን ነው፡፡
ያሳወቁንን እያመሰገንን፣ ያላወቅነው እንዲገልጥልን እንለምናለን፡፡
ይላል ዲን ዳንኤል ክብረት ከአዲስ አበባ ኢትዮጵያ ፣ ማነህ እዚያ ጋር ተረኛ ቀጥል ። አሳየው ላላየው ። አከተመ ።
ያዝ እንግዲህ. ምድረ ግሪሳ ሁላ.!
"እኔ ግን እላለሁ !!! እምዬ ኦርቶዶክስ አንቺ እናትዓለም ፤ የእነ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ፣ የእነ ቅዱስ አትናቴዎስ እና ቅዱስ ቄርሎስ የእነ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፣ የእነ ቅድስት አርሴማ ፣ የእነ አቡነ ተክለሃይማኖት ፣ የእነ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ፣ የአባ ሳሙኤል ዘዋልድባና የአቡነ አረጋዊ ሃይማኖታቸው የሆንሽ ንጽህት ተዋሕዶ ሃይማኖቴ ሆይ ! ብረሳሽና ብከዳሽ ቀኜም ትርሳኝ፣ ትክዳኝም ። ባላስብሽና ባልሞትልሽ ምላሴ ከጉሮሮዬ ይጣበቅ ። ሳለጎበድድ ሳለከዳሽ እንድኖር አምላክሽ ይርዳኝ ። ይህን ባለደርግና ሳልጮህልሽ ዝም ብዬ ብሞት ስሜ ከህይወት መጽሐፍ ይደምሰስ ።
"ጌታ ሆይ! ከዚህ በፊት በሆነው ፤ አሁንም እየሆነ ባለው ነገር እና ወደፊትም በሚሆነው ነገር ፤ ክብሩን ሁሉ አንተ ውሰድ ።" አሜን. !
"ድንግል ሆይ እናቴ ! አዛኝቱ ዛሬም እንደትናንቱ ቅደሚ ከፊት ከኋላዬ "
ይህንን ጦማር ዲን ዳንኤል ጻፈው መግቢያውንና ወቀሳውን እኔው ራሴ በእጄ ጻፍኩት ። +4915217428134 ደግሞ የቫይበር ፣ የኢሞና የኋትስአፕ መልእክቶችን የምቀበልበት የእጅ ስልኬ ነው ።
ሻሎም.! ሰላም.!
ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
ግንቦት 16/2009 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ ።

ማን በቀደሰው ማይ ማን ይጠመቃል? ( በዲን አባይነህ ካሴ)


Share ~በማድረግ ላላየ እናሳዩ ፤ ላልሰማም እአሰሙ ።
Comment ~በመስጠት በድርጊቱ ላይ ተወያዩ ።
Tag ~ በማድረግ በፉጨት የተሻሉ ሰዎችን እንጥራ ።
...ዛሬ ደግሞ ተረኛው ዲን አባይነህ ካሴ ነው ። አንደበተ ርቱዕ ነው ። ሲጽፍ በብዕሩ ፣ ሲናገር በአንደበቱ ገዢ ነው ። ጀግና ጀግና ልጆችን በላይ በላዩ መውለድ የማይታክታት እምዬ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ይኸው ዛሬ ደግሞ ልጇ ዲን አባይነህ ካሴ እኔም ጥያቄ አለኝ ብሎ ከተፍ ብሏል ።
ከዚህ ቀደም በፀረ ተሃድሶው ትግል ወቅት ግንባር ቀደም ታጋይ የነበረ መሆኑም በሁላችን ዘንድ ይታወቃል ። ለእነ " ታዴ " ተሃድሶ " የቀደመ የክብር ስማቸውን ከመዝገብ ቤት አቧራውን አራግፎ አውጥቶ ፤ ከኪዳነወልድ ክፍሌ መዝገበቃላት ውስጥ ፈልጎ " ሐራ ጥቃ " የሚለውን የቀደመ ስማቸውን ይጠሩበት ዘንድ ያስታወሰን ወንድማችን ነው ።
ዲን አባይነህ ካሴ ፦ በሙያው ኢንጂነርም ነው ። በገዛ ገንዘባችን ፣ ረቡብን ፣ በሚለው ስብከቱም ይታወቃል ። ለቅድስት ቤተክርስቲያን በርካታ መጻሕፍትን ያበረከተ ምርጥ የተዋሕዶ ልጅ ነው ።
አሁን ጀነራሎቹ እየመጡ ነው ። እንደኔ አይነቱ ከ " ፈንጅ ማምከን " ያልዘለለ ሙያ የሌለው ሰው አሁን ከሜዳው ላይ ገለል የሚልበት ጊዜም እየመጣ ነው ። በእኔ ቀፋፊ ጩኸት አንገታችሁን የደፋችሁ ወገኖች አሁን የጠላት ወረዳን ነጻ የማድረጉ ሥራ በመልካም ሁኔታ እየሄደ ስለሆነ ሥፍራውን ለሚመለከታቸውና ለሚገባቸው ሰዎች የመልቀቂያ ጊዜዬ እየደረሰ ነው ። እናም ትንሽ ጊዜ ነው የምትታገሱኝ ።
በአባ ኃይለማርያም ሺህ ሞት ላይ ጥያቄያችን ይቀጥላል ። አናቋርጥም ። የቅዱስ ሲኖዶሱ አባላት በድጋሚ እንዲያጤኑትም እንመክራለን ።
"ኤጲስ ቆጶስ በሚሾምበት ቀን ሰዎች ሁሉ ይገኙ። ሕዝብና ካህናት መስክረውለት ይሾም።..."ፍትሐ ነገስት በእንተ ኤጲስ ቆጶሳት ፤ አንቀጽ ፭፡፻፩ በሚለው መሠረት ህዝብና ካህናት ያልመሰከሩለት ግለሰብ አይሾምብንም ። አከተመ ።
በተለይ ይህ የህዝብ ፍላጎት ተጥሶ ይሄ መቅደሳችንን ያስደፈረ ግለሰብ በእንቢተኝነት ቢሾም ። በተለይ
ብፁዕወቅዱስ አባ ማትያስ
 ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ
 ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ
 ብፁዕ አቡነ ገብርኤል
 ብፁዕ አቡነ ቀለሚንጦስ
የሕዝቡን ጩኸትና ተማጽኖ በመናቅ መቅደስ አርካሹ ዶ/ር አባ ኃይለማርያምና በመንግሥት ትእዛዝ እንዲሾሙ የሚፈለጉት አባ ተክለሃይማኖት ንጉሤ እንዲሾሙ እንዲያ መድከማችሁና ቤተ ክርስቲያንን ለውድቀት የሚዳርግና ሕዝበ ክርስቲያኑን የሚያሳዝን ድርጊት እንዲፈጸም አብዝታችሁ ስትታትሩ የታያችሁ በመሆኑ በዚህች ቤተ ክርስቲያንና ተከታዮቿ ላይ በጠላትነት የተነሣችሁ መሆናችሁ ይታወቅ ። እናም አዝነንባችኋል ። ሆኖም ግን አሁንም አልረፈደም ሥርዓተ ሲመቱ ከመፈፀሙ በፊት የሕዝብ ቅሬታ ተሰምቶ ጉዳዩን በድጋሚ እንዲታይ እንጠይቃለን እያልን በተቃውሞአችን እየቀጠልን በቀጥታ ወደ ዲን ኢንጅነር አባይነህ ካሴ ጦማር እንገባለን ። መልካም ንባብ ።




.......የጠቅላይ ቤተ ክህነት ምክትል ሥራ አስኪያጁ አጥማቂ ፍለጋ ከአባቶቻቸው ይልቅ ወደ ፕሮቴስታንቶች ማዘንበላቸውን በራሳቸው አንደበት ተናገሩ፡፡ በሰዓሊተ ምሕረት ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን እንደተከናወነ የተነገረው ቅብዓት አይሉት ጥምቀት በእርሳቸው ብቻ ሳይኾን በፓትርያርኩ ቡራኬ ሰጪነት የተከናወነ መኾኑ አነጋጋሪ ነው፡፡
እኛ እነርሱን ስናጠምቅም ይሁን ስንቀባ ብንገኝ ደግ በኾነ፤ አንድ ፓስተር ብድግ ብሎ አንድን በቁምስና ማዕርግ ያለ የቤተ ክርስቲያን ከፍተኛው አስተዳደር ውስጥ ተዋናይ የኾነን ሰው ሲቀባም ይሁን ሲያጠምቅ ማየት ከየት እንደመጣ እስካሁን ማንም አልነገረንም፡፡ ለጊዜው የነገሩ ሙሻዙር ወደ ም/ሥ/ አስኪያጁ ያጠንጥን እንጂ ዋናው ተጠያቂ መኾን ያለባቸው ፓትርያርኩ ናቸው፡፡ ሰውየው አድርግ የተባሉትን አድርገው ይኾናል፡፡ ይህም መለካዊነታቸውን ከሚያሳብቅባቸው በቀር ከተጠያቂነት ነፃ ያደርጋቸዋል ማለት አይደለም፡፡
እንኳን በማዕርገ ቁምስና በምእመን ደረጃም እንዲህ ያለ የሚፈጽም በሌለባት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ይህን የኃፍረት ካባ ሊያከናንቡን መቁረጣቸው ብርቱ ጽዩፍ አድራጎት ነው፡፡ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን ለማን እንዴት መቼ እንደሚፈጸም በጉልህ የምታስተምርን ቤተ ክርስቲያን በቅጽሯ ውስጥ ነውረኛ ሥራ በማድረግ መሠማራት አደጋው ቀላል አይደለም፡፡ "የጥፋት ርኵሰት በማይገባው ስፍራ ቆሞ ብታዩ፥ አንባቢው ያስተውል" ያለውን ልብ እንበል፡፡ ማር ፲፫፥፲፬።
ለመኾኑ እርሳቸው አሉ እንደሚባለው ጉዳዩ የተከናወነው በውኃ ነው ከተባለ፤ ጥምቀቱ ለልጅነት ነው ወይስ ለፈውስ? ቤተ ክርስቲያን የሰጠቻቸውን ልጅነት የት ጥለውት ይኾን? አሞኝ ነው ካሉ ደግሞ ጠበል ቤት እንጂ ኪታ ለባሽ ፓስተር ይዞ ወደ መቅደስ መግባትን ምን አመጣው? ከሰባቱ ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን በየትኛው አንቀጽ እንደሚወድቅም ሊነግሩን ይገባል፡፡ ኢኩሚኒካል ግንኙነትን ስለማጠናከር ነው ከተባለም በምሥጢር ተካፋይነት የሚፈጸም አይደለም፡፡
ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንኳን ለመናፍቅ ትምህርተ ክርስትናን በመከታተል ላይ ያሉ ባለ ተስፋዎችን በቅዳሴ ጊዜ ምሥጢር ለመካፈል የበቁ አይደሉምና (ማለትም አልደረሱምና) ፃዑ ብላ ታሰናብታለች፡፡ እኒህን ጳጳስ አደርጋለሁ ብሎ . . . መነሣት ነገ ደግሞ ማንን አምጥተው በማን እንዲቀቡ ይኾን? ከአባቱ ውጭ ሌላ አባት መፈለግ . . .
በሰውየው ላይ ብዙ ችግር እንዳለ እየታወቀ ብዙ ጊዜ በዝምታ ታለፉ፡፡ አሁን ብለው ብለው በአደባባይ ቤተ ክርስቲያንን የማይመጥኑ መኾናቸውን በይፋ አጋለጡ፡፡ የሰውን ዲዘርቴሽን ግጥም አድርገው ገልብጠው ፒኤች ዲ አለኝ ሲሉ ኖሩ፡፡ ዝም ተባሉ፡፡ በሆለታ ገብርኤል አካባቢ ያለባቸውን ብዙ ነውረኛ ሥራ ሲሠሩ ኖሩ ዝም ተባሉ፡፡ አሁን ደግሞ ሌላ . . .
በቅርቡ ቅዳሴ ረዘመ ብለው በሸገር ሬድዮ ሲነዛነዙ የነበሩት ፓትርያርክ አሁን ደግሞ እንዲህ ባለ ተግባር ላይ መሰለፋቸው ሒደቱን በጥሞና የሚያየው አካል ይፈልጋል፡፡ የእናት ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ እንዲህ በዋዛ በዋዛ እየታለፈ መቀጠል የለበትም፡፡ የሃይማኖት ጉዳይ ቀስ በቀስ እንዲሸረሸር ብርቱ ጥረት የሚደረግ ይመስላል፡፡ በሰዓሊተ ምሕረት በተደረገው ይህ ኩነትም እንደ ደኅና ነገር ጳጳስ አስከትለው የደብር አለቆችን ጠርተው ታዳሚ ኾኖ መገኘት ምን ይሉታል? ቅዳሴው እንዲያጥር የሚከራከሩት ሰው ቀድሞም ቢኾን ምክሩን ያገኙት ከአንድ የፕሮቴስታንት ፓስተር እንደነበር ነግረውን ነበር፡፡ አሁን ደግሞ ፓስተሮቹን ወደ ቤተ መቅደስ ይዘዋቸው ገቡ፡፡
በአሁኑ የግንቦቱ (፳፻፱) ሲኖዶስ ጉባኤ መካከል አንዱ ተነሥተው "መሠረት ስብሐት ለአብ መናፍቅ አይደለም" ብለው ድምፅ አሰምተዋል መባሉ ሌላው አነጋጋሪ ጉዳይ ነው፡፡ አለማወቅ እንዲህ ካለ ድፍረት ያደርሳል፡፡ ክርስቶስ አማላጅ ነው ብሎ የቅዱሳንን ሥራ ለእግዚአብሔር ሰጥቶ የተናገረን ሰው መናፍቅ አይደለም ብሎ መከራከር ምን ይሉት ጥብቅና ነው፡፡ ሰውየው ሔደው የሙጥኝ ብለው የተጣበቁበት ድርጅት ምን ብሎ የሚያስተምር እንደኾነ በገሃድ እየታወቀ ለክርክር መሰናዳት ምን ይባላል?
የኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያንን አቋም የሚሸራርፉትን በጥብቅ የሚቃወሙት አቡነ ቄርሎስ የሰጡት ምላሽ አንጀት አርስ ነው፡፡ የሚቅበዘበዝ ሀሳብ የሚያመጡትን እዚያው መገሠፁ የተገባ ለመድረኩ የሚመጥን ነውና፡፡ ግን እንዲሁ በቀላሉ መታየት አለበት ተብሎ መወሰድ የለበትም፡፡ ያንን ቃል የተናገሩት ጳጳስ ናቸውና በሀገረ ስብከታቸውም ብዙ ሃይማኖታዊ ውዝግብ እየፈጠሩ የሚገኙ ናቸውና ጉዳያቸው ለብቻ መታየት ይገባዋል፡፡ እኒህን ጳጳስ ሰውየው ራሱ ቢሰማቸው እንዴት በሳቀባቸው፡፡ ጥብቅናውን አይፈልገውም፡፡ ይብላኝ ለእርሳቸው እንጂ በአደባባይ ማንነቱን ደጋግሞ የተናገረ "ምስጉን" መናፍቅ ነው፡፡ ታዲያ ለሞተ ሰው ጥብቅና መቆሙን ምን አመጣው? ነገር ዝም ብሎ አይመዘዝምና ደጋግሞ ማጤኑ ይበጃል፡፡
እነዚህ ሦስት ጉዳዮች በለበጣ የሚታዩ አይደሉም፡፡ ይታሰብባቸው!
ይለናል ዲን ኢንጅነር አባይነህ ካሴ.!! ማነህ ባለ ሳምንት ጅግና የተዋሕዶ ልጅ ተረኛ ቀጥል.! ቀጥል.!
ያዝ እንግዲህ. ምድረ ግሪሳ ሁላ.!
"እኔ ግን እላለሁ !!! እምዬ ኦርቶዶክስ አንቺ እናትዓለም ፤ የእነ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ፣ የእነ ቅዱስ አትናቴዎስ እና ቅዱስ ቄርሎስ የእነ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፣ የእነ ቅድስት አርሴማ ፣ የእነ አቡነ ተክለሃይማኖት ፣ የእነ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ፣ የአባ ሳሙኤል ዘዋልድባና የአቡነ አረጋዊ ሃይማኖታቸው የሆንሽ ንጽህት ተዋሕዶ ሃይማኖቴ ሆይ ! ብረሳሽና ብከዳሽ ቀኜም ትርሳኝ፣ ትክዳኝም ። ባላስብሽና ባልሞትልሽ ምላሴ ከጉሮሮዬ ይጣበቅ ። ሳለጎበድድ ሳለከዳሽ እንድኖር አምላክሽ ይርዳኝ ። ይህን ባለደርግና ሳልጮህልሽ ዝም ብዬ ብሞት ስሜ ከህይወት መጽሐፍ ይደምሰስ ።
"ጌታ ሆይ! ከዚህ በፊት በሆነው ፤ አሁንም እየሆነ ባለው ነገር እና ወደፊትም በሚሆነው ነገር ፤ ክብሩን ሁሉ አንተ ውሰድ ።" አሜን. !
"ድንግል ሆይ እናቴ ! አዛኝቱ ዛሬም እንደትናንቱ ቅደሚ ከፊት ከኋላዬ "
ይህንን ጦማር ዲን ዳንኤል ጻፈው መግቢያውንና ወቀሳውን እኔው ራሴ በእጄ ጻፍኩት ። +4915217428134 ደግሞ የቫይበር ፣ የኢሞና የኋትስአፕ መልእክቶችን የምቀበልበት የእጅ ስልኬ ነው ።
ሻሎም.! ሰላም.!
ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
ግንቦት 17/2009 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ ።

LikeShow More Reactions
Comment

Tuesday, 23 May 2017

ቁርቁር ሲኖዶስ

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ትላንትና ወይም ዛሬ የተፈጠረች አይደለችም፡፡ ሲኖዶሳዊ ታሪኳ ግን ቁርቁር ነው፡፡ ሲኖዶሳዊ አበቃቀሏ ቁርቁር በመሆኑ ሲኖዶሳዊ ገጽታዋም የተቆረቆሩ ከተሞች ገጽታ ዐይነት ነው፡፡ ለነገሩ ድሮ ድሮ ቁርቁር ከተማ እንጂ ቁርቁር ሲኖዶስ አልነበረም፡፡ ቁርቁር ከተማዎች ለመኖራቸው ብዙ ምሳሌዎችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ለጊዜው ከጎጃም የበዛብህ መዲና ማንኩሳ፤ ከሲዳማ ተፈሪ ኬላ ምስክሮቼ ናቸው፡፡ እኒህ ከተማዎች እግረ መንገድ በንጉሣዊ ትእዛዝ የተፈጠሩ ናቸው፡፡ እናም ዛሬ ዛሬ ቁርቁር ከተማዎች አልፈው በዘመናች ነገሥታት ትዕዛዝ የሚፈጠሩ ቁርቁር ሲኖዶሶች እየበዙ ነው፡፡ ቁርቁር ከተሞች በዋናነት ተፈጥሯዊ ሒደትን ተከትለው አይፈጠሩም፡፡ አብዛኛው ጊዜ አፈጣጠራቸው የነገሥታቱን ምጣኔ ሀብታዊ እና ፖለቲካዊ ኀይልን ማዕከል በማድረግ ነው፡፡ በቁርቁር ከተሞችም እንዲከትሙ የሚደረጉት በብዛት ከነገሥታቱ ጋር ማኅበረ ፖለቲካዊ ተዛምዶ ያላቸው ሰዎች ናቸው፡፡
ሲኖዶሳችንም አበቃቀሉ እንዲሁ ነው፡፡ ሲኖዶሳዊ የአበቃቀል ሒደትን ተከትሎ ያላደገ እንደመሆኑ የቄብ ስብስብ ነው፡፡ በዚህ የአበቃቀለ ሒደት ውስጥ በሃይማኖት ብሔርተኝነት ራስን ለመቻል የተጋደሉ አበው ቢኖሩበትም፥ የንጉሡ የፖለቲካ ኀይል ሚዛን ፍላጉት ግን ማዕከላዊ ነበር፡፡ የብልጭታ ያህል ጥቡዓን አበውም ቢኖሩበትም፥ ንጉሡም ፖለቲካዊ ፍላጎቶቼን ያስጠብቁልኛል ያሏቸውን አበው እንዲካተቱ ማድረጋቸው አይጠረጠርም፡፡
በዚሁ የታሪክ አዙሪት የቀጠለው ሲኖዶሳችን መለካዊነትን በተልዕኳዊ ቅርጽ ያዳበረ ይመስላል፡፡ በተለይ ደግሞ በዚህ ዘመን መንግሥታዊ ፈቃዳትን መፈጽም ሲኖዲሳዊ ተልእኮ ወደ መሆን ያደገ ይመስላል፡፡ መንግሥትም ፈቃዴን ያስፈጽሙልኛል ያላቸውን አባቶችን ለማስረግ የሚጋደለውን ያህል፤ሲኖዶሳችንም ፈጻሜ ፈቃድ የሆኑትን አበው አካቶ ለመሔድ እጅግ የተጋ ነው፡፡ መንግሥት በግልጽ አባ ሠረቀ ወልደ ሳሙኤል፣ አባ ኀይለ ማርያም መለስና አባ ተክለ ሃይማኖትን ሲኖዶሱ በኤጴስ ቆጶስነት አካቶ እንዲሔድ የተለያዩ ግፊቶችን አድርጎ ነበር፡፡ ቅዱስነታቸውም ይህን መንግሥታዊ ፈቃድ ለማስፈጸም ከአቶ ካሣ ተክለ ብርሃን ጋር በመሆን አስመራጭ ኮሜቴውን ማወያየታቸው አብነታዊ ማሳያ ነው፡፡ አባ ሠረቀ ከፓትርያርኩ ጋር በነበራቸው አለመግባባትና ይህን ተከትሎም በአቶ ካሳና በፓትርያርኩ መካከል በተፈጠረው ክፍተት ነጥበው ሲቀሩ፥ አባ ኀይለ ማርያም መለስና አባ ተክለ ሃይማኖትን ተካትተው ሔደዋል፡፡ በርግጠኝነት አባ ሠረቀ ከፓትርያርኩ ጋር ቅራኔ ውስጥ ባይገቡ ኖሮ ተካተው መሔዳቸው አይቀርም ነበር፡፡ ሲኖዶሳችን በመለካዊነት-በፈጻሜ ፈቃድነት አይጠረጠርምና፡፡
ቁርቁር ሲኖዶስ የቁርቁር ተሿሚዎች ስብስብ እንደመሆኑ መጠን ፥ የኤጴስ ቆጶሳት የምርጫ ሥርዐቱም ስሪታዊ ነው፡፡ በስሪታዊ የምርጫ ሥርዐት ደግሞ በአንድ በኩል የምርጫ ሕጉ ጉቦ ለተቀበሉባቸውንና ለመንግሥታዊ ተልዕኮ ለተመለመሉት እጩ ኤጴስ ቆጶሳት ማለፍ ጋሬጣ መሆኑ ከታወቀ፤ ጋሬጣ የሆነው የሕግ አንቀጽ እንዲወጣ ይደረጋል፡፡ ለምሳሌ በአሁኑ የኤጴስ ቆጶሳት የምርጫ ሕግ ለጥቆማ እና ለምርጫ ቋንቋ እና ዘውግ መስፈርት ነበሩ፡፡ነገር ግን ጉቦ ለተቀበሉባቸውንና ለመንግሥታዊ ተልዕኮ ለተመለመሉት እጩ ኤጴስ ቆጶሳት ማለፍ ጋሬጣ እንደሆነባቸው የተረዱት ቀንደኛ አማሳኝ እና መለካዊ ሊቃነ ጳጳሳት ተረባርበው ከምርጫ ሕጉ እንዲወጣ አድርገዋል፡፡ ለአንቀጹ መውጣት ግን ምክንያት ያደረጉት አሰቀድመው የተቀዎሙትንና በኋላ ደግሞ ለሽፋን የተጠቀሙበትን ፥ ‹‹ አካባቢና ቋንቋ በመስፈርት መካተቱ ከመንፈሳዊ አሠራርና አንድነትን ከማጽናት አንጻር ችግር ያስከትላል፡፡ ›› የሚለውን ነው፡፡ እውነታው ግን እርሱ አነበረም፡፡ ሕጉ በአንድ ገጽታው በአቡነ እስጢፋኖስ የተደራጀው (በጎልህ መገለጫው) የመለካዉያን ጳጳሳት ስብስብ እንዲመረጡ ለሚፈልጓቸው ለአባ ተክለ ሃይማኖት ዘጋቤላ እና በሌላው ገጽታ ደግሞ በአቡነ ኤልያስ የተደራጀው (በጎልህ መገለጫው) የአማሳኝ ጳጳሳት ስብስብ እንዲመረጡ ለሚፈልጓቸው ለአባ ሔኖክ ሁኔታውን ማመቻቸት ነበር፡፡ በዚህ ሕግ መሠረት አባ ተክለ ሃይማኖትም ሆኑ አባ ሔኖክ የተወዳደሩበት ሀገረ ስብከት ቋንቋቸውም ሆነ ዘውጋቸው አይደለም፡፡ ሰለዚህ ቋንቋና ዘውግን የተመለከተው አንቀጽ መደምሰስ ነበረበት፡፡ እነርሱም እንዲካተቱ ተደረገ፡፡
በሌላ በኩል ድግሞ ስሪታዊ የምርጫ ሥርዐት ለገዳማዊ ሕይወት እና ለትምህርት ደረጃ ተገቢውን ዋጋና ክብር ሰለማይሰጥ፥ በገዳማዊ ሕይወታቸውም ሆነ በትምህርት ደረጃቸው የተመሰከረላቸውን እየገፈተረ፤ በገዳማዊ ሕይወታቸውም ሆነ በትምህርት ደረጃቸው ነቀፋ ያለባቸውን አካቶ ይጓዛል፡፡ መንግሥታዊ ድጋፍ አላቸው ያላቸውን ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጪ ሲያካትት፤ መንግሥታዊ ድጋፍ ሳይኖራቸው በሊቃውንት እና በምዕመናን ዘንድ ቅቡል የሆኑትን የሚገፈትር ነው፡፡ ይህ ማለት በገዳማዊ ሕይወታቸው የተመሰከረላቸውን እና በትምህርት ደረጃቸው እጅግ የላቁትን ሊቀ ሊቃውንት እዝራን በአጣማጅ አወዳድሮ፤ በገዳማዊ ሕይወታቸውም ሆነ በትምህርት ደረጃቸው ነቀፋ ያለባቸውን አባ ተክለ ሃይማኖትን ያላጣማጅ በብቸኝነት አወዳድሮ ኤጴስ ቆጶስ ማድረግ ማለት ነው፡፡ ወይም ደግሞ መንግሥታዊ ድጋፍ ያላቸውን አባ ተክለ ሃይማኖትን ወይም አባ ኀይለ ማርያምን ሹሞ፤ መንግሥታዊ ድጋፍ የሌላቸውንና ቅቡል የሆኑትን ሊቀ ሊቃውንት እዝራን አለመሾም ነው፡፡
ስሪታዊ ምርጫ ቁርቁር ተሿሚዎችን መቀፍቀፍ ባሕርይው ነው፡፡ አሁን ያለው ሲኖዶሳችን የዚህ መንስኤ እና ተግብሮት ነው፡፡ ከስሞኑ የተካሔደው ምርጫ ደግሞ የተግብሮቱ ክትያ ነው፡፡ ሲኖዶሳችን ከዚህ ባሕርያዊ መገለጫው አኳያ፥ በአምስተኛው ዘመነ ፕትርክና የተሾሞ መለካውያን ኤጴስ ቆጶሳትንም ሆነ አሁን በእነዚሁ መለካውያን የተቀፈቀፉትን አዲሶቹን መለካውያን እጩ ኤጴስ ቆጶሳት አካቶ መሔዱ ግድ ነበር፡፡ ነገሩ ከእንክርዳድ ስንዴ አይለቀምምና ነው፡፡
ምእመኑ ለሚቀጥለው ትውልድና ስለነገይቱ ቤተ ክርስቲያን ህልውና ሲጨነቅ፤ አንዳንዶቹ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ዛሬ ሊያገኙ ስለሚጓጉት ተጨማሪ ሹመት፣ ቤት፣ መኪና እንቅልፍ አጥተው ይጨነቃሉ፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ሰብዓዊ ገጻቸው ወደ ማኅበራዊ ትምክህተኝነት እንዲዘቅጡ አድርጓቸዋል፡፡ ምጣኔ ሀብታዊ ቅርምት ውስጥም ከቷቸዋል፡፡ ውጤቱ ደግሞ ለቤተ ክርስቲያኒቱ መተረማመስ አስተዋጽኦ ያደረጉ የጥፋት ኃይሎች ዛሬ ደግሞ በእነሱ ትከሻ ላይ ታዝለው እንዲመጡ ረድቷቸዋል፡፡ የሚያስጨንቀውም የእነርሱ መምጣት ሳይሆን የአባቶቻችን መለካዊነታቸው አይሎ የተውኔቱ አባላት መሆናቸው ነው፡፡ በዚህ መልኩ በሩ የተከፈተላቸው አተራማሽ ኃይለ ግብር ቁስላችንን ዘወትር እንዳሰፉት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱን ከኦርቶዶክሳውያን መዳፍ ውስጥ ፈልቅቀው በማውጣት እና ዘላለም በሰማዕትነት ከአከበሯት አባቶቿ ብብት ውስጥ በመስረቅ አይሆኑ ሆና እንድትኖር ግዴታ ይጥሉባት ዘንድ ሢመታዊ መደላደልን ተቀዳጁ፡፡
ይህ ሲሆን ግን የእነ አቡነ ቄርሎስ፣አቡነ ቀውስጦስና አቡነ ገብርኤል ከለላ ሰጪነት፤ ይህቺ ቤተ ክርስቲያን ጨርሶ ወደ ጥፋት፣ ወደ ውድመት፣ ወደ ሞት የመሔዷ ማስረጃ አይደለምን? በርግጥ እንዲህ ዓይነቱን የኋላ ሩጫ ከጀመርነው ይኼውና ሃያ ስድሰተኛውን ዓመት ጀምረነዋል፡፡ ሆኖም ግን የሰማዕታቱ ቤት፣ የነጻዎቹ ሊቃውንት ቤተ ክርስቲያን እስካሁን ፈርሳ አላበቃችም፡፡ በእርግጥ ግን ተዋርዳለች፡፡ ውርደቷም በእርሷ ስም ያሉት መሪዎቿ መዋረድ ነው፡፡ እነሱ ምንም ይሁኑ ምን ፍርዱን ከእግዚአብሔር የሚያገኙት ሲሆን፥ የሚያሳዝነኝ ግን ለቤተ ክርስቲያኒቱ ክብር መጣኝ ባልሆኑ ድርጊቶቻቸው በሌላው ዓለም ፊት ተዋርደው የኛኑ ቤተ ክርስቲያን ማዋረዳቸው ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያኒቱ ከእነሱ መኖሪያ ቤት ክብር በታች ስትታይ ምን ይሰማችኋል? የቆራጦቹ ሰማዕታት ቤት፣ የነጻዎቹ ሊቃውንት ቤት ተዋረደች አያሰኝም?በርግጥ ነገሩ ሁሉ የተበላሸው አሁን አይደለም፡፡ ሢመተ ጵጵስናው ክብር ሲያጣ፣ የምልመላው መስፈርት ቦታ ሲያጣና ከሕግ ውጪ ያለ ምእመናን ይሁንታ ሲታደል ነው፡፡
በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው ቅዱስ ሲኖዶስ፣ የመንበረ ሐዋርያት ወራሽ የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ፣ ከማንኛውም የቤተ ክርስቲያኒቱ የሥልጣን መዋቅር ሁሉ የበላይ የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ፣ በእንዲህ ዓይነቱ መለካዊ ግብር መታጀሉ እጅግ ያሳዝናል፡፡ ለእኔ የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቁርቁር ሲኖዶስ አባላት ገጽ ይኼ ነው፡፡ የእናንተን ገጻዊ ትንታኔ ደግሞ በእናንተው መንገድ አሳዩኝ፡፡ ለእኔ ግን አሁንም ቁርቁራዊ ገጹ አይሏል፡፡ መንፈሳዊ ገጹ ኮስምኗል፡፡ የዘወትር ምኞቴም ሆነ መሻቴ እንደ ዘውድ የተቆጠረው ቆብ ተገቢውን ቦታና ሰው እንዲያገኝ ነው፡፡ የዘወትር ሕልሜ እውነት ሸባቢው “ዘውድ” ወልቆ እውነት አናጋሪው ቆብ እንዲጫን ነው፡፡ ይህም እውን የሚሆነው ሲኖዶሳችን ከመለካዊነት ወይም ከቁርቁርነት ወደ ኦርቶዶክሳዊ ኵላዊነት ሲለወጥ ብቻ ነው፡፡ ይህንንም እናፍቃለሁ፡፡

Friday, 19 May 2017

የእኔ የዘመዴ ስጋትና ኑዛዜዬ ።

የእኔ የዘመዴ ስጋትና ኑዛዜዬ ።

★ ★ ★ ★ ★
ጎበዝ አደጋ ላይ ነኝ ✔ የልጆቼን ነገር አደራ.! ገዳዮቼ ጀርመን ገብተዋል ፤ መረጃው ለጠበቃዬ ደርሷል ፣ ጉዳዩ በህግ ተይዟል ። ነገር ግን ምንም አይመጣም ፣ በእኔ በኩል ሁሉን ለመቀበል ዝግጁ ነኝ ። እናት ቤተከርስቲያን ፍርሃትን አላስተማረችኝም ። የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስን ገድሉን ሳነብ ስባረክበትም ኖሬ ደግሞ ልፍራ.!! ወጊድ በለው ።
✔Share ~ Share ~ Share ~ Comment✔
✔ልብ ብላችሁ ስሙኝ አድምጡኝም ። ስተፈልጉ ቅዠት ስትፈልጉም ትንቢት ብነው ብላችሁ አድምጡኝ ።
✔ በተለይ የትግራይ ልጆች ጆሮ ሰጥታችሁ ስሙኝ ።
✔ የባሌ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳሳት የነበሩት ታላቁ የሃይማኖት ገበሬ ብፁዕ አቡነ ሰላማ በረከታቸው ይደርብንና ከታች የተናገሩት ቃለ ምዕዳን ሰምተን እንጠቀምበት ።
ውድ ኢትዮጵያውያን ይልቅ ከወራት በፊት ቀመር ተሠርቶለት የተጠናቀቀውን የአባ ኃይለማርያምንና የአባ ተክለሃይማኖትን በመንግሥት ትዕዛዝ ቀድሞ መመረጥ እያነሳን በከንቱ ጨጓራችን መላጡንና ጊዜ መፍጀቱን አቁመን ዳይ.! ዳይ.! ዳይ.! ወደ ቀጣዩ አጀንዳ በአስቸካይ እንግባ ።
ልብ በሉ ፈረንጆቹ መጀመሪያ እንዲህ አሁን ኢየሱስ ጌታ ነው የሚል ፉከራ በየአደባባዩ ሊያሰሙን እኛን እምነት የፋራ ነው ፣ እግዚአብሔር የሚባል ነገር የለም ፣ አሉንና እኛንም ፋራ አትሁኑ እግዚአብሔር የለም በሉ ብለው ሰበኩን ፣ ፍልስፍናቸውንም ጫኑብን ። አዳሜ እውነት መስሎን እግዚአብሔር የለም እንድንል አደረጉን ፤ ፓጋንም ሆነን እንደ እንስሳም መኖር ጀመርን ። ጾም ቀረ ፣ ጸሎትም ተረሳ ፣ ማስቀደስ ፣ ካህን ማክበርም ተተወ ፣ መስቀል ተናቀ ፣ ፀበል ተጠላ፣ መዕተብ ተበጠሰ ።
ቀጠሉና ኢትዮጵያውያን ሞትን የማይፈሩት ፣ ለሃገራቸው ሲሉ ባዶ እጃቸውን ሽመል ይዘው ሚሳኤል ከጫነ ሠራዊት ጋር ተዋግተው የሚያሸንፉት.?? ምን ቢሆኑ ነው.?? ብለው ተመራምረውና አጥንተው ሲያበቁ አስኳሉን አገኙት ። ይኸውም ምንድ ነው ያልን እንደሆነ ፤ ኢትዮጵያውያን ጀግና የሆኑት ፣ በእግዚአብሔር ማመናቸው ፣ ቅዱሳት መጻህፍትን መመርመራቸው፣ ገድለ ጊዮርጊስን ፣ ገድለ መርቆሬዎስን ፣ ገድለ አቡነ አረጋዊን ፣ ገድለ አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ፣ ገድለ ክርስቶስ ሠምራን ፣ ገድለ እስጢፋኖስን በማንበባቸው ምክንያት የሰማዕታት ህይወት ስለተዋሃዳቸው ፤ ልምምዱም ስላላቸው ነው ሞትን የማይፈሩት የሚል ሆኖ አገኙት።
ከዚያማ ምን ይጠየቃል ትውልድ ፈጠሩ ፣ ገድል ከቤተክርስቲያን ይውጣ ፣ ድርሳን ምን ያደርጋል ፣ አዋልድ መጻህፍት ምን ይሠራሉ ፣ የሚሉ ትውልዶችን ፈጠሩ ። ይኸው ዛሬ ወጣቱ የዚህ ተንኮል ምርኮኛ ሆኖ የራሱ የሆነውን ጥሎ አናንቆና ሰድቦ አረፈው ። አሁን እድሉን አጥተው እንጂ እድሉን ቢያገኙ በአንድ ቀን ሁሉን ነገር ድምጥማጡን አውጥተው መጻህፍቱን በሙሉ አቃጥለው ቢጨርሱ እንዴት ደስተኛ በሆኑ ነበር ።
ደግሞ እንዲህ አሉን ፤ ጤፍ መብላት አይጠቅምም ፣ በጤፍ ውስጥ ምንም አይነት ለሰውነት የሚጠቅም ማዕድን የለበትም ፣ ዝም ብሎ ሰጋቱራ ነገር ነው ፣ የፈረስና የከበት ምግብ እንጂ የሰው ልጅ ሊበላው የሚችለው ምግብ አይደለም። እግር ኳስ ተጫዋቾቻችሁ እንዲህ ቀጫጭን የሆኑት የማይረባውን ጤፍና የጤፍ እንጀራ በመብላታቸው ምክንያት ነው ተባለና ሰው ጤፍን እንዲንቅ ተደረገ ፣ ጤፍ ተጠላች ትውልዱ ፈረንጅ ለመሆን ሲል የፈረንጅ ምግብ ነው ወደ ተባለ ነገር ፊቱን አዞረ ። ጤፍ ይመገብ በነበረ ጊዜ ጤነኛ የነበረው ኢትዮጵያዊ ሁሉ አሁን የፈረንጅ የተባለ ምግብ ሲመገብ ጊዜ የሚፈልገውን ውፍረት አገኘ ፣ ፊቱም ወዛ አለ ፣ ቀላም አለ ፣ ፈረንጁንም መሰለ ፤ ነገር ግን በተቃራኒው ደግሞ በሽተኛ ሆነ ። በኢትዮጵያ ታሪክ በምንመገበው ምግብ እና በአመራረት ዘይቤያችን ምክንያት ሰው ሁሉ በከንሰር ፣ በጉበት ፣ በኩላሊት ፣ በስኳር እና በጨጓራ ምክንያት ይረግፍ ጀመር ፣ የሆስፒታል አልጋዎች ጠፍተው ዜጎች ኮሪደር ላይ ተሰቃይተው የሚሞቱባት ሀገር ሆነች ።
እና አሁን ጤፍን ከዘረፉን በኋላ ዛሬ የእነሱ ሰዎች ጤፍን በመመራመር ፕሮፌሰር ተባሉበት ፣ በጤፍ ውስጥ ያለውንም አስደናቂ ንጥረ ነገሮች በሙሉ እየተደነቁ መልሰው ይተነትኑልን ጀመር ፣ ዛሬ በአውሮፓና በአሜሪካ ጤፍን መመገብ በጤና ለመኖር እንደዋስትና ተቆጠረ ። እኛ ግን እንረግፋለን ። እነሱ አንድ ኪሎ ጤፍ የወርቅ ዋጋ ተምነውለት መልሰው በውድ ይሸጡለታል ።
እነሱ ፊደል መቁጠራችንን ፣ በቄስ ትምህርት ቤትም ማለፋችንን እንደ ፋርነት እንድንቆጥረው አደረጉን ። ግዕዝ ማጥናት ፣ መነጋገር ፣ መጻፍ የፋሮች ፣ የኋላ ቀሮችም ነው ብለው እኛን አስጣሉን ። በጎን ግን ዘረፉን ፣ አስዘረፉን ፣ ቋንቋውንም የሚያስተምሩበት ዩኒቨርስቲዎችን ከፍተው ግእዝን ያጠናሉ ፣ በግእዝ የተጻፉ መጻህፍትንም በመመርመር የተደበቁ ጥበቦችን ያፈልቁበት ጀመር ።
እኛን ጤና አዳምን እና ዳማከሴን አስጥለው እነሱ ጀሶና ከኖራ የተሰራ እንክብል አዋጡን ። በጦርነት ያልጠፋን ህዝቦች እነሱ በሰው ሰራሽ ችግሮች ፈጁን ።
2ሺ ዘመን የቆየውንና ስንታመም የሚጸልይልን ፣ ስንጣላ የሚያስታርቀንን ፣ በ40 እና በሰማንያ ቀናችን ከምስጢረ ጥምቀት የሚያካፍለንን ፣ ወንጌል ሰብኮ ፣ ቀድሶ አቁርቦ ስንሞት በጸሎተ ፍትሃት የሚሸኘንን የራሳችንን ካህን እንድንጠላ ፣ እንድንንቀው ፣ እንዳንሰማው አደረጉን ፣ እነሱ ግን ፓስተር የሚባል ስያሜ የተሰጠውን ጎረምሳ እንደ ኳስ የሚያንቀረቅበንን ፣ በአደባባይ የሚያዋርደንን ፣ የሚጫወትብንን ፣ የሚቀልድብንን ፣ ከኮሜዲያን በላይ የሚያስቀንን የእኛን ካህን የሚተካ አምጥተው አስቀመጡብን፣ አለማመዱን ፣ አሁን ትውልዱ እንደ ፓስተር የሚፈራው እና የሚያከብረው ሰው በዚያች ምድር ላይ ያለ ማንም የለም ።
የባህል ልብሳችንን አስወልቀው ታይትና ጅንስ አስታጠቁን ፣ የጸጉር አሰራራችንን ሳይቀር እንድንጠላው ተደረግን ፣ ትውልዱ ከራሴ ጀምሮ ፣ ጠጪ ፣ አመንዝራ ፣ ጫታም እና ሰካራም እንድንሆን አደረጉን ። ነፈዝ ሆንን ፣ ጀዘብን ፣ ከንቱና የማንረባ ሆንን ፣ አሁን በቁማችን ሞተናል ። ስለ ሀገር መጠየቅ ፋርነት ነው ። ማጨስ ፣ መጠጣት ግን ፋሽን ፣ ነው ዘመናዊነት ሆኖ ትውልዱ ላሽቆ እንዲቀመጥ ተደረገ ። ሐሰት ነገሠች ፣ እውነት ሀገር ለቃ ተሰደደች ። መሪዎች ሳይቀሩ ፣ ሚዲያው ሳይቀር ፣ የሃይማኖት አባቶችና ታላላቅ ሰዎች ሳይቀሩ ሐሰተኞች ሆነን ተገኘን ።
አሁን ትውልዱ ለምለሟን እና ውስጧ አረንጓዴ የሆነውን ሀገር ጠልቶ እግሬ አውጪኝ ብሎ እየተሰደደ ነው ። ካህናት ፣ ዲያቆናት ፣ መነኮሳት ፣ ባህታውያን ፣ ማየት የሚያስጠላው ትውልድ እንዲፈጠር በብርቱ ደከሙ ። ለጊዜው ሲያዩት የተሳካ መስሎ ታይቷል ። እግዚአብሔር ግን አሳልፎ አይሰጠንም ።
አደዋ ላይ ፣ ገጉንደት ላይ ፣ ምጽዋ ላይ ነጮቹን ድል መንሳታችን ቂም አስቋጥሮብን ይኸው ዋጋ እያስከፈለን ነው ። ሀሰት የሚል ካለ ይምጣ. ፣ ።
የምንወደውን ነገር ሁሉ እንድንጠላ እየተደከመ ነው ። ባንዲራውን ብትሉ ፣ አንድነትን መመርጥ ብትሉ ፣ እጅግ አይወደድም ፣ የተበታተነ ፣ የማይግባባ ፣ የማይተማመን ዜጋ እንዲፈጠር በብርቱ ተለፋ ፣ እናም እየተሳካ ነው ። በኢትዮጵያዊነቱ ሳይሆን በብሄሩ የሚመካ ትውልድ ተፈጠረ ፣ ጠቡ አሁን ፍሬ እያፈራ ነው ። ሰሞኑን በመቀሌ ያየነው የባህርዳር ከነማና የመቀሌ ስፓርት ደጋፊዎች ጠብ የጤና አይመስልም ። ከተለመደው እና በእስፓርት ሜዳ ከምናየው ጠብ የተለየ ነው ። ማንነትን መሰረት ያደረገ ጸብ ነው ።
ፈረንሳይ ፣ ቤልጂየም ፣ ጣሊያን ፣ ስዊዘርላንድ ፣ ኦስትሪያ እና ሆላንድን አይቻለሁ አሁንም በጀርመን እገኛለሁ ። አንዳቸውም መታወቂያቸው ላይ በጎሳው የሚጠራ አላየሁም ፣ ተሳስቼ ከሆነ እታረማለሁ ። የእኛ ግን አሰቃቂ ነው ። እግዚአብሔር ይጠብቀን ።
የመጨረሻው ታርጌት ታቦተ ጽዮንን ፍለጋ ነው ። ትውልዱ እንደፋሽን የያዘውን ነገር ተመልከቱልኝ ከደቡብ ክልል የጀመረው ሃይማኖትን የማስቀየር ዘመቻ አሁን አሁን መሃል ሀገሩን ጥሶ የአማራውን ክፍል አልፎ ትግራይ ገብቷል ። ኤርትራ አስቀድማ እንድትገነጠል ተደርጓል ። አሁን ኢትዮጵያዊ ማንነቱን ሙልጭ አድርገው አጥበው አዲስ የጎሳ ማንነት የተላበሰ ፣ አዲስ ሃይማኖት የሚከተል ፣ ሀገር ፣ ባህል ግድ የሌለው ትውልድ ተፈጥሯል ።
መቀሌ በተሃድሶ ፕሮቴስታንቶች እየታመሰች ነው ። ሽሬ ተሃድሶዎቹና ኦርቶዶክሶቹ የሞት ሽረት ትግል እያደረጉ ነው ። አዲግራት ደግሞ " አዲግራትን ለኢየሱስ " የሚል ፕሮጀክት ቀርጸው የሚንቀሳቀሱ ዲያቆናትና የሰንበት ተማሪዎችን በመመልመል በሱዳን ካርቱም ተመልምለው በአዲስ አበባ ሰልጥነው አዲግራት ድረስ ሄደው ስልጠና የሚሰጡ የተሃድሶ አባላትን ማሰማራት ጀምረዋል ። የሚገርመው አዳራሹን የሚፈቅድላቸው መንግሥት ሲሆን ፈቃዱን የሚጠይቁላቸው ደግሞ ፕሮቴስታንቶች ናቸው ። መረጃውን ሰሞኑን ጠብቁኝ ። በአይናችሁ ታይቱላችሁ ።
አሁን የቀረው ማነው ያልን እነደሆነ አክሱም ጽዮን ማርያም ። በመጨረሻም ሀገሩ በሙሉ ኦርቶዶክስ ተዋህዶን እንዲጠላ ይደረግና ፣ ሃይማኖቱንም በሙሉ ወደ ፕሮቴስታንትነት ይቀይርና ፣ ታቦት አያስፈልግም ፣ ይውጣ የሚል ትውልድ በንደንብ ከፈጠሩ በኋላ ታቦተ ጽዮንን ከአክሱም በመውሰድ ሦስተኛውን መቅደስ ሠርተው ሲጨርሱ የለ ግርግር ታቦት የሚጠላው ትውልድ በክብር ያስረክባቸዋል ማለት ነው ።
ስለዚህ በቀጣይ በኢትዮጵያ እንዲህ ይሆናል ። በዋነኝነት ማኅበረ ቅዱሳን በውድም ሆነ በግድ እንዲፈርስ ይደረጋል። በአረጋውያኑ ጳጳሳት ምትክ አዳዲስ የተሃድሶ አራማጅ የሆኑ ወጣት ጳጳሳት ቦታውን እንዲይዙ ይደረጋል ። የሰንበት ትምህርት ቤቶች እንዲፈርሱና በፕሮቴስታንታዊ ቅኝት በተቃኙ የተሃድሶ ሰራዊት ይተካል ።
የካህናትን ክብር የሚያጎድፉና ካህናት እንዲጠሉ የሚያደርግ በአደባባይ የሚሰክር ፣ የሚጠጣ ፣ የሚዘርፍ እንግዳ መነኩሴና ካህናት ይፈጠራሉ ።
በዚህ መሃል ግማሹ በአዲሱ እምነት ይማረካል ። ቤተመቅደሱ ላይ የጥፋት ርኩሰት ይቆማል ። ይህንን ጉድ የሚጋፈጡ ጥቂቶች ፣ ይታሰራሉ ፣ ይገደላሉ ፣ ይሰደዳሉ ። አንዱ ሌላውን እንዳይረዳው እንኳ አስቀድሞ በግልፅ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በጎሪጥ እንዲተያይና እንዳይተማመን በመረረ የዘር ጥላቻ እንዲዋጥ ተደርጓልና ማንም ማንንም አይረዳም።
በአሩሲ አኖሌ በፈጠራ ታሪክ የአያቶችሁን ጡት የቆረጠው ይሄውልህ ተብሎ ያደገው ኢትዮጵያዊ ኦሮሞ ለበቀል ከመሮጥ በቀር ሌላ የሚያቆመው ያለ አይመስልም ። ለረጅም ዘመናት በአንድነት ኢትዮጵያን የገነቡት ጎንደሬ ኢትዮጵያውያንና የትግራይ ኢትዮጵያውያን በግድ ጥላቻን እየተጋቱ እንዲያድጉ ስለተደረጉና አሁን ደግሞ ይበልጥ ዙሩን እያከረሩት በመምጣታቸው አያድርስና በትግራይ አንድ ችግር ቢፈጠር ፣ ደግሞም በጎንደር አንድችግር ቢፈጠር ለመረዳዳት የሚደረግ ነገር እንደ ቀድሞው ፈጣን አይመስለኝም ። ይሕ ሁሉ ሲሆን የፕላኑ አውጪዎች ግን ቁጭ ብለው ይሳቃሉ ። እዚህ ጀርመን ከህዝቡ መሃል ሃይማኖት አልባው ይበዛል ። ፓስተሮቹ ግን ህዝባቸውን ሃይማኖት አልባ አድርገው እነሱ ሻንጣቸውን ጠቅልለው ከእነ ፓስተር ዳዊት ጋር ለመሥራት ኢትዮጵያ ከትመዋል ።
በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ውስጥ ሃብታም ለመሆን ከፈለግክ ፕሮቴስታንት መሆን ብቻ ነው የሚጠበቅብህ ። ሥራ የለም ግን ሀብት አላቸው ። ንግድ ቀዝቅዟል ፕሮዎቹ ግን የናጠጠ ኑሮ ይኖራሉ ። የእኛዎቹ እነ በጋሻውና ያሬድ አደመን እንኳ ተመልከቱልኝ ፣ የ53 ሚልየን ብር ፋብሪካ በአንድ ጀንበር ከፍት. አድረዋል ። ተሃድሶና ጴንጤ ከሆንክ የሚገጥምህ እጣ ይኽ. ነው ።
ወዳጆቼ መፍትሄ ግን አለው ።
መፍትሄውም በመጀመሪያ ልባችንን ክፍት አድርገን በዙሪያችን ምን እየተካሄደ እንደሆነ ማየት ይገባናል ። ከዚያም ለፍቅርና ለእርቅ እንዘጋጅ ። ውይይቱን በቤተሰብ እንጀምር ።
አሁን በተፈጠረው ነገር አኩርፋችሁ ከቤት እንዳትቀሩ አደራ ፣ እናንተ ከቀራችሁ ፤ ቤተክርስቲያኑን ባዶውን ስለሚያገኙት ይወርሱናልና በምንም ተአምር እንዳትቀሩ ። አደራ ከቤተክርስቲያን እንዳትቀሩ ። በምንም መልኩ ቢሆን ድንጋይ መወርወር ፣ ጮክ ብሎ መሳደብ የተዋሕዶ ልጆች መገለጫ አይደለምና እንዳታደርጉት ተጠንቀቁ ። ዝም ብሎ እውነትን ይዞ መሟገት ብቻውን በቂ ነው ። አሸናፊም ያደርገናል ። ከሁሉ አስቀድመን ግን ሁላችንም ንስሐ እንግባ ፣ ወደ ሰንበት ትምህርት ቤት እንቅረብ ። እንወያይ እንደማመጥ ፣ እንከባበር ፣ እንዋደድ ።
ከመካከላችን አንድ ሙሴ እንምረጥ ። ወይም መርጦ እንዲሰጠን ወደ እግዚአብሔር እንጸልይ ፣ ሱባኤ እንግባ ፣ አባቶቻችንም እኛም በድለንሃል ብለን እናልቅስ ። አይናችን እያየ በታሪክ እርስ በእርስ በሃይማኖት ምክንያት አደጋ ላይ ከመውደቃችን በፊት እንምከር ፣ እንመካከር ።
እንደ አርቲስት ቴዲ አፍሮ አይነቱን ህዝቡን በኢትዮጵያዊነት የፍቅር ገመድ አስተሳስሮ አንድነትን የሚሰብክ የፍቅር ሰዎችን ያብዛልን ።
በእኔ በኩል የትግራይ ልጆችን አደጋው ከባድ እንደሆነ ለማስረዳት ብዙ ደክሜያለሁ ፣ ቀላል የማይባሉ የትግራይ ልጆችም ይህንን ተንኮል የምትሠራው ህውሓት ናት የሚል ሃሳቤን በማቅረቤ ምክንያት በብዙዎች ዘንድ የትግራይን ህዝብ እንደምጠላ ተደርጌ ፕሮፓጋንዳ ስለተሠራብኝ ሊሰሙኝ እየፈለጉ ነገር ግን ዘረኛ እየመሰልኳቸው ጆሮ ዳባ ልበስ ሲሉኝ ቆይተዋል ። እኔም ድርቅ ብዬ ህዝብና ፓርቲ አንድ አይደለም ። እናም እባካችሁ ግድየላችሁም ብዬ ተጨቃጭቄ ዛሬ ላይ ቁጥሩ ቀላል የማይባል የትግራይ ልጆች ከጎኔ ቆመዋል ። መረጃዎች በሰነድ የተደገፉ ወደ እኔ በመጉረፍ ላይ ናቸው ።
አሁንም የትግራይ ልጆች ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ ከልባችሁ ስሙኝ አድምጡኝም ። ከአነጋገሬ ስህተት ሳትረዱኝ ቀርታችሁ የተቀየማችሁኝ ካላችሁ ፤ እንዲያው በተሰቀለው መድኃኒዓለም ፣ በታቦተ ጽዮን ፣ በአክሱሟ ማርያም ፣ በጻድቁ አቡነ አረጋዊ ፣በአብርሃወአጽብሃ ይዣችኋለሁ ፣ በአካል ከእናንተ ጋር ባልሆንም እግራችሁ ስር ተደፍቼ እለምናችኋለሁ ። አጥፍቼ ከሆነ ማሩኝ ፣ ይቅርም በሉኝ ።
ፖለቲካ ሃላፊ ነው ። ፖለቲከኞችም እንዲሁ ። የማታልፍ እና ጌታ እስኪመጣ የምትቆየው ሀገር ናት ። እባካችሁ እባካችሁ ተለመኑኝ ፣ ኢትዮጵያን ታደጓት ።
ስለ እኔ ኢትዮጵያዊነት ለማወቅ ከሀገር እስክወጣ ድረስ በአክሱም ከተማ ውስጥ ከመንግሥት ተረክቤ አስተምራቸው የነበሩትን የአክሱም የድሃ ልጆች ቤተሰቦችና የከተማውን ከንቲባ ጽ/ቤት ጠይቁ ። ደብረ ዳሞ ሂዱና ፣ አቡነ መድኃኒነ እግዚም ሂዱና ፣ አብርሃ ወአጽብሃ ፣ ገርአልታ አቡነ ይምአታ ፣ ማኅበረ ዶጌና ራሷ አክሱም ጽዮን ሄዳችሁ ዘመድኩን ማነው ብላችሁ ጠይቁ ። በሊቢያ የተሰውትን ሰማዕታት ቤተሰቦች ኢንቲጮና ገዛ ገረሥላሴ ሄዳችሁ ስለ እኔ ጠይቁ ። ይነግሯችኋል ።
እኔ አሁን ብዙም የደኅንነት ስሜት አይሰማኝም ሆኖም ግን ሌላ አማራጭ ስለሌለኝ የማይቀረው ነገር እስኪመጣ ድረስ እስከመጨረሻዋ ደቂቃ ድረስ የቻልኩትን ያህል ለመታገል እሞክራለሁ ። እይታዎቼንም ወደ እናንተ አቅም በፈቀደ መጠን ለማድረስ እሞክራለሁ ።
በስልኬ ላይ ስለምጽፍ እንጂ በቻልኩት መጠን ቶሎ ቶሎ በመጻፍ ወደ እናንተ ባደርስ ምንኛ በወደድኩ ነበር ። ለመድረስ እሞክራለሁ ። የሚፈጠረው አይታወቅምና ድንገት የማያምር ነገር መጥፎ የሆነም ዜና በእኔ ላይ ቢፈጠርና ብትሰሙ የለጆቼን ነገር.! አደራ.! አደራ.! አደራ.! አደራ በሰማይ አደራ በምድርም አደራ ። የእናንተ ልጆች ናቸው ። አሳድጉልኝ ፣ አስተምሩልኝ ፣ ለቁምነገር አብቁልኝ ። አሁን እየደረሱኝ ያሉት ዛቻዎች ደስ አይሉም ። ነገር አንድ ጊዜ የነብሩን ጭራ ይዧለሁና መልቀቅ ብሎ ነገር አይታሰብም እዚህ ጀርመን ድረስ እዚሁ ሆነው የተቆጡብኝ ስላሉ ምንም። ምንም አይነት ነገር በእኔ ህይወት ላይ ቢፈጠር አደራ ሃይማኖታችሁን ከመጠበቅ ወደ ኋላ እንዳትሉ ። ታቦተ ጽዮንም በእኔና በእናንተ ዘመን እንዳትነጠቅ ። ቅዥት ቢመስልም ግን እውነታው ይሄው ን. ።
በቀጣይ ጽሑፌ በእስከ አሁኑ ሂደታችን ተሸንፈናል ወይስ አሸንፈናል የሚለውን ለማየት እንሞክራለን ።
የኢትዮጵያ ቡናና ፣ የቅዱስ ጊዮርጊስ ደጋፊዎች በሚያሰሟት የጋራ ዜማቸው እንሰነባበት ።
አሆሆ አሃሃ መሸነፍ የለም.!
 አሆሆ አሃሃ መሸነፍ የለም.!
 አሆሆ አሃሃ መሸነፍ የለም.!
 አሆሆ አሃሃ መሸነፍ የለም.!
እንኳንም ተሰደድኩ ፣ እንኳንም አስጨንቀው ከሀገሬ አስቀሩኝ ። ስለእውነት እንነጋገር ከተባለ አሁን እንደምፈነጨው በሀገሬ ብሆን እፈነጭ ነበርን? ። መንፈራገጤ አይቀርም ነበር ። ነገር ግን ኮማንድ ፖስቱ ዋጋዬን ሰጥቶ አደብ ያስገዛኝ ነበር ። ወይ አንቀጽ ጠቅሶ ሸዋሮቢት ፣ ወይ ደግሞ አከናንቦ ሰማይ ቤት ይልከኝ ነበር ። አሁን ግን ለጊዜው ሰላም ወረዳ ነው ያለሁት ፤ እናንተ መረጃዎችን ላኩልኝ እኔ እንደሚሆን እንደሚሆን አደርገዋለሁ። እስከ ጊዜው ድረስ ።
" እኔ ግን እላለሁ !!! እምዬ ኦርቶዶክስ አንቺ እናትዓለም ፤ የእነ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ፣ የእነ ቅዱስ አትናቴዎስ እና ቅዱስ ቄርሎስ የእነ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፣ የእነ ቅድስት አርሴማ ፣ የእነ አቡነ ተክለሃይማኖት ፣ የእነ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ፣ የአባ ሳሙኤል ዘዋልድባና የአቡነ አረጋዊ ሃይማኖታቸው የሆንሽ ንጽህት ተዋሕዶ ሃይማኖቴ ሆይ ! ብረሳሽና ብከዳሽ ቀኜም ትርሳኝ፣ ትክዳኝም ። ባላስብሽና ባልሞትልሽ ምላሴ ከጉሮሮዬ ይጣበቅ ። ሳለጎበድድ ሳለከዳሽ እንድኖር አምላክሽ ይርዳኝ ። ይህን ባለደርግና ሳልጮህልሽ ዝም ብዬ ብሞት ስሜ ከህይወት መጽሐፍ ይደምሰስ ።
አንቺ ቅድስት ቤተክርስቲያን ሆይ.! ጌታ በደሙ የመሰረተሽ ነሽና ደሙ ይፍረድልሽ ። አከተመ በቃ.!
"ጌታ ሆይ! ከዚህ በፊት በሆነው ፤ አሁንም እየሆነ ባለው ነገር እና ወደፊትም በሚሆነው ነገር ፤ ክብሩን ሁሉ አንተ ውሰድ ።" አሜን. !
"ድንግል ሆይ እናቴ ! አዛኝቱ ዛሬም እንደትናንቱ ቅደሚ ከፊት ከኋላዬ "
ፌስ ቡክ What's on your mind? ስላለኝ ይህንንም ራሴው ከአእምሮዬ አቅንቼ በእጄ ጻፍኩት ። +4915217428134 የቫይበር ፣ የኢሞና የኋትስአፕ መልእክቶችን የምቀበልበት የእጅ ስልኬ ነው ።
ሻሎም.! ሰላም.!
ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
ግንቦት 11/2009 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ።

ከብፁዓን አባቶቻችን ለእምዬ ተዋሕዶ ልጆች የተላከ የደስታ መልእክት


★ ★ ★ ★ ★
✔Share ~ Share ~Share በማድረግ ይኅንን መልእክት ላልሰማ አሰሙ ። ላልደረስው አዳርሱ ። ✔ Comment ~ Comment ~ Coment በመስጠት ደግሞ አዳዲስ ሃሳብ አፍልቁ ።
✔እባካችሁ አትደውሉልኝ ። መልእክት በቻ ጻፉልኝ ። እረ ልፈነዳ ነው ። ተባበሩኝ ጓደኞቼ.!!
✔በመሃል እየገቡ ያልሆነ የብስጭትና ከርእሳችን ውጪ አጀንዳውን ለመጠምዘዝ የሚሞክሩትን እንደበፊቱ አልታገሳቸውም ። መብቱ በእጄ ስለሆነ ይህን ከመሰለ ጮማ የሆነ ጦማት ከሚኮመኩሙበት ገበታ አስወግዳቸዋለሁ ። እመ አምላክ ምስክሬ ናት ።
✔ አሁን እኛ ስለ ራሳችን የምንመካከርበት ግዜ እንጂ የእነሱን ቅርሻት የምንጠርግበትና እሱንም ለማጽዳት ጊዜ የምናጠፋበት ወቅት ላይ አይደለንም ። አራት ነጥብ ። እስቲ ወንድ የሆንክ አሁን እኔ ፔጅ ላይ አፍህን ክፈት ። አሳይሃለሁ ። Block በተባለ ሰይፍ ነው ቆርጬ ከፔጄ ላይ የማስወግድህ ። ሰምተሃል.!
✔ትግላችሁ እንዳይቆም.! በፍፁም ኦርቶዶክሳዊ ጨዋነትና ጥበብ አጠናክራችሁ ቀጥሉ ተብላችኋል ።
✔ ብረትን መቀጥቀጥ እንደጋለ ነውም ብለዋል ። እናም የእምዬ ልጆች ዝግጁ ናችሁ. !???
የተከበራችህ ውድ የእምዬ ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስቲያን እምነት ተከታዮች በሙሉ ። የቅድስት የቤተክርስቲያናችንም ሆነ የኢትዮጵያ ሀገራችን ትንሳኤ የቀረበ መስሎ ይሰማኛል ። ደግሞም እንደዚያም ነው ።
በሰሞኑ በእኔና በእናንተ የተቀናጀ እና ውጤታማ ፍፁም ኦርቶዶክሳዊ ትግል የተነሳ አስደናቂ እና የሚያኮራ ተግባር መፈጸማችን ይታወቃል ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ታሪክ እንዲህ አይነት የሚያስደንቅ ፣ የሚያኮራ ፣ እንባና ሲቃ ፣ እልህና ቁጭት ተፈጥሮ በያገባኛል ባዮችና ፣ መብቴነው በሚሉ የተዋህዶ ልጆች አስደማሚ ተሳትፎ ምክንያት ታሪካዊ እንቅስቃሴ በማድረግ ወርቃማ ገድል ፈጽመናል ።
በዘህ እንቅስቃሴ መንግሥት ደንግጧል ፣ መናፍቃን ተበሳጭተዋል ። ሌላው ቢቀር የጀርመን ዜግነት ያላቸው ነጭ ጸሐፊዎች እንኳን " የዘመድኩን ውሸት " በማለት በአካል ባያውቁኝም በስማበለው በሰሙት መጥፎና ወሽመጥ ቆራጭ ዜና አማካኝነት ተናደው አርቲክል አዘጋጅተው ለንባብ አብቅተዋል ። ከመናፍቃኑ ወገን አባ ኃይለማርያም እና አባ ተክለሃይማኖት እንዲሾሙ ፕሮቴስታንቶችና ፓስተሮች ሳይቀሩ የፆም አዋጅ እስከማወጅ ደርሰዋል ። ለጊዜውም ቢሆን አባ ኃይለማሪያ በሴራና በተንኮል ። አባ ተክለሃይማኖት በጠመንጃ አፈሙዝ በግልጽ መሾማቸው በተሰማ ጊዜ በእኛ በኦርቶዶክሳውያን ዘንድ የድንጋጤ ፣ የተስፋ መቁረጥ ፣ የሀዘን ፣ የመከዳት ፣ የመሸጥ ፣ ስሜት ሲያድርብን ፣ በአንጻሩ ደግሞ በተሃድሶዎቹና በመናፍቃኑ ዘንድ ስሜታቸውን መቆጣጣጠር አቅቷቸው በድስታ የዓለም ዋንጫ እንደበላ ሀገር ሲፈነጥዙ ታይተዋል ።
ለማንኛውም ይህ የመናፍቃኑ ደስታ እና የእኛም ሀዘን ብዙም አልቆየም ። ወዲያው በድርጊቱ የተበሳጩ የተዋሕዶ ልጆች ለእረፍት ለምሳ ወጥተው የነበሩትን አባቶች በስልክም በአካልም መቆሚያ መቀመጫ በማሳጣት በታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ አንድ በሐሰትና በቁማር ያውም በጨበጣ የተሾመን ጳጳስ ሹመቱ ይቆይ አስብለናል ። በዚህ ነው ፈረንጆቹ ፣ ተሃድሶዎቹና ፕሮቴስታንቶቹ የተበሳጩት ። እኛ ግን ደስ ቢለንም ገና ትግላችንን አልጨረስንም ። አይደለም እንዴ.??? ዋሸሁ እንዴ.???
አሁን አብዛኛዎቹ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት በሁኔታችን ፣ በምእመናን ትብብር ፣ ጫና መፍጠር ፣ በእጅጉ ኮርተዋል ። በተለይ ልጅ እግሮቹ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ከሚገባው በላይ ደስተኞች ሆነው ተገኝተዋል ። እናም በዚህ ምክንያት ምእመናን ድርሻቸውን እንዲህ አውቀው ፍፁም በሆነ መንፈሳዊ ስነስርዓት አሁን ካለው በበለጠ ሁናቴ ተጠናክረው ከቀረቡ የማይለወጥ ነገር የለም ብለዋል ።
ትናንት ተሰባስበው መረጃ የሰጡኝና መልእክቱን ለህዝብ አስተላልፍልኝ ያሉት ብፁዓን አባቶች አንተ ዘመዴ አንደበት ስለሆንከን ፣ መተንፈሻችንም ስለሆንክ እጅግ አድርገን እግዚአብሔርን እናመሰግነዋለን ብለዋል ።
አሁን ከዚህ ፖስት በመቀጠል በእዚህ ጉባኤ ትልቁን ሴራ በመሥራት ዶር አባ ኃይለማርያምና አባ ተክለሃይማኖት እንዲመረጡ ግፍ የሰሩ በተለይ ሁለት አባቶችን አዳፋሪና አንገት የሚያስደፋ ተግባር ለህዝብ ይፋ አድርገው ብለው ልከውልኛል ። ያበጠው ይፈንዳ ።
እኔም ይሄን እንደመግቢያ አድርጌ የተንኮለኞቹን አባቶች ስምና ፎቶ ፣ መጀመሪያ የእጅ ስልካቸውን እሱን አላነሳ ካሉና ከዘጉ ደግሞ የቢሮና የቤት ስልካቸውን እለጥፈዋለሁ ። አሁን ይህን 2009 ዓመተ ምህረትን ቤታችንን ጽድት አድርገን 2010 ዓመተ ምህረትን ተንኮለኛ ፣ ሴረኛ ፣ ሙሰኛ ፣ ዘማዊ ፣ ፖለቲከኛና ፣ ካድሬ ካህናትና መነኮሳትን መስመር አስይዘን የደስታ ፣ የፍቅር ጉዞ እንጀምራለን ።
ከእንግዲህ ወዲያ መደራደር የለም ፣ እስቲ 60 ሚልዮን የሚገመተውን የእምነቱን ተከታይ የመንግሥት ወታደሮች ሲያስቆሙት እናያለን ።
ይሄ ሌባ ሌባው ወንበዴና ዘራፊ ሆኖ ሳለ በደብር አስተዳዳሪነት ፣ በፀሐፊነት ፣ በገንዘብ ቤት ፣ በቁጥጥጥር ስም ተመራርጠው በየደብሩ የተሰገሰጉ ሌቦችንም መንጥረን እናወጣለን ። አንዳቸውንም አትፍሯቸው ። እያንዳንዳቸውን እናውቃቸዋለን ። ትናንት ከገጠር ሲመጡ ምን ይመስሉ እንደነበሩ እናውቃቸዋለን ፣ ፎሮፎር የወረሰው ጭንቅላት ፣ ወርጭ ያደረቀውና ጭርት ያበላሸው ፊት ፣ የተበጫጨቀ ኮትና ነጠላ ፣ ሙጀሌና የሞላው ባዶ እግር ፣ እንቅፋት የነቀለው ጥፍር ፣ መግል የቋጠረ እግር ፣ እከክ የወረሰው ገላ ይዘው ነው ወደ እኛ የመጡት ። እያንዳንዱን እናውቀዋለን። ከሁሉም ጋር እንተዋወቃለን ። ከሁሉም ጋር ። አዳሜ እከኩን ካራገፈ በኃላማ ፣ ሙጀሌውን ካወጣ በኋላማ አሁን በዘረፈን ገንዘብ ተንደላቅቆ መኖሩ ሳያንስ የክህደት መርዙን አያቀረሽብንም ። በፍፁም ። ቱ ሞተናታላ. ። በእኛ ዘመን ቤተክርስቲያን አትፈርስም ። እንዲህ አይነት ቆሻሻ ታሪክም በዘመናችን አይፈፀምም ።
አሁን ከጥቂት ሰዓታት በኋላ እንደየ አደገኝነታቸው እና እንደነበራቸው አፍራሽ ሚና ያርፉ እንደሆን እንዲያርፉ ፣ የማያርፉ ከሆነ ግን ቀልድ ስለሌለ እረፍት የሚነሳ ተቃውሞ የምናነሳባቸውን የከዱንና ከመንግሥት የደኅንነት ኃይሎች ጋር እስከ ሌሊቱ 8 ሰዓት በመዶለት በጥርነፋ ገብተው ሌሎቹ በፁዓን አባቶች ላይ ተፅእኖ የፈጠሩ አባቶችን ክፉ ስራ ተራ በተራ ለማየት እንሞክራለን ።
ጎበዝ ጨከን ብለን በድፍረት ካልተነጋገርን ለፀላ ምንም አይነት መፍትሄ እንደሌለን እወቁ ። አማራጭ የለንም ። ቤተክርስቲያን የህእብ ናት ። እናም ለህዝቡ የሚሾሙትን አባቶች መምረጥ ያለበት ህዝቡ እንጂ ኢህአዴግ አይደለም ። ኢህአዴግ ከፈለገ ዶር አባ ኃይለ ማርያምንም ሆነ አባ ተክለሃይማኖትን በለመደው መንገድ ይጠቅሙኛል ብሎ ካመነበት ለፓርላማ አቅርቦ ያወዳድራቸው ። አለቀ ። በቃ ይኸው ነው ። አከተመ።
ምነው ሸዋ.! አለ ሌሊን ። ሆሆይ!
" እኔ ግን እላለሁ !!! እምዬ ኦርቶዶክስ አንቺ እናትዓለም ፤ የእነ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ፣ የእነ ቅዱስ አትናቴዎስ እና ቅዱስ ቄርሎስ የእነ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፣ የእነ ቅድስት አርሴማ ፣ የእነ አቡነ ተክለሃይማኖት ፣ የእነ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ፣ የአባ ሳሙኤል ዘዋልድባና የአቡነ አረጋዊ ሃይማኖታቸው የሆንሽ ንጽህት ተዋሕዶ ሃይማኖቴ ሆይ ! ብረሳሽና ብከዳሽ ቀኜም ትርሳኝ፣ ትክዳኝም ። ባላስብሽና ባልሞትልሽ ምላሴ ከጉሮሮዬ ይጣበቅ ። ሳለጎበድድ ሳለከዳሽ እንድኖር አምላክሽ ይርዳኝ ። ይህን ባለደርግና ሳልጮህልሽ ዝም ብዬ ብሞት ስሜ ከህይወት መጽሐፍ ይደምሰስ ።
አንቺ ቅድስት ቤተክርስቲያን ሆይ.! ጌታ በደሙ የመሰረተሽ ነሽና ደሙ ይፍረድልሽ ። አከተመ በቃ.!
"ጌታ ሆይ! ከዚህ በፊት በሆነው ፤ አሁንም እየሆነ ባለው ነገር እና ወደፊትም በሚሆነው ነገር ፤ ክብሩን ሁሉ አንተ ውሰድ ።" አሜን. !
"ድንግል ሆይ እናቴ ! አዛኝቱ ዛሬም እንደትናንቱ ቅደሚ ከፊት ከኋላዬ "
ፌስ ቡክ What's on your mind? ስላለኝ ይህንንም ራሴው ከአእምሮዬ አቅንቼ በእጄ ጻፍኩት ። +4915217428134 የቫይበር ፣ የኢሞና የኋትስአፕ መልእክቶችን የምቀበልበት የእጅ ስልኬ ነው ።
ሻሎም.! ሰላም.!
ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
ግንቦት 11/2009 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ።

ፕላን B ን በአስቸኳይ እንጀምረው.!! የኔታ ሺህ ሞቱ እንኳን ቀረብዎ.!

Image may contain: 1 person, standing, horse and outdoor
የኔታ እና እኔ.! ቅዱስ ያሬድ ወደተሰወረበት ቅዱስ ያሬድ ገዳም ስንሄድ ለማስታወሻ የተነሳነው ፎቶ ነው ። እንዲህ በነፃነት በጉባኤ ቤታቸው ሚልዮን ተተኪ ሊቃውንት ማፍራት እየቻሉ የምን ሹመት የምን ጵጵስና ነው.??

ጎበዝ እንዳንዘናጋ !!
መተማመን እንደሁ
ውኃ በልቶታል
★ ★ ★
ይህ ጦማር በቀጣይ ሁላችንም ምን ማድረግ እንዳለብን እና እናንተም በምን ዙሪያ መዘጋጀት እንዳለባችሁ የሚጠቁም ጦማር ነው ።

✔የኔታ ዕዝራ ሀዲስ እንኳንም አልተመረጡ.! እንኳንም ቀረብዎ.!
✔ አንድነት እውነትም ኃይል ነው ።
✔ ውድ ጓደኞቼ የምን እጅ መስጠት ነው.!! የምን መብሰልሰል ነው አሁን ረጋ እንበልና፤ ቆም ብለን በማሰብ ፤ በጨዋ ደንብ በፍጥነት ወደ ፕላን B መንቀሳቀስ ነው ነው ያለብን ።
እመኑኝ.! ከምሬ ነው የምላችሁ መቼም በታሪክ ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ በዚህ ባሳለፍነው ወር ውስጥ ሃይማኖታችንን በተመለከተ ያደረግነው ትግል ለብዙዎች መልእክት ያስተላለፈ ነበር ። ዛሬ የአባ ኃይለማርያምና ፣ የአባ ተክለሃይማኖት መመረጥ ትንሽ ያበሳጨን ቢመስልም በጨዋታው ግን አሸናፊዎቹ እኛ ነበርን ።
ተመልከቱ በስልክ ጠሪ ብቻ ሆቴሎች ለግሪሳ ሁላ የመሰብሰቢያ አዳራሽ እንዲከለክል አደረግን ። ያውም ከአንድም ሦስት ኢንተርናሽናል ሆቴሎችን ይቅርታ አስጠይቀን ዝግጅት አስዘረዝን ። ይሄ ታላቅ ድል ነው ። አሰግድን የመሰለ አስቸጋሪ ግሪሳ እንዲወገዝ ታላቅ አስተዋፅኦ ያደረግነው እኛው ነን ። ይሄም ለእኛ ታላቅ ድል ነው ።
በዚህ ጉባኤ ምክንያት ብዙ ሰው ነቅቷል ፣ ተቀስቅሷል ፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ በቤተክርስቲያን ላይ ፤ እየተደረገ ስላለው ደባና ሴራ እንኳን እኛ ኢትዮጵያውያን ይቅርና ፦
፩ኛ ፦ ትውልደ ኢትዮጵያውያን የሆኑ ቤተ እስራኤላውያንና
፪ኛ ፦ ሀገር ወዳድ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ወንድሞቻችን በሚገባ ስለ ጉዳዩ አውቀዋል ።
፫ኛ፦ መንግሥትም የትግል ስልታችን አስደምሞታል ። ተኩሶ የሚገድለው የለ ፣ ቂሊንጦና ሸዋሮቢት ዝዋይና ቃሊቲ የሚያጉረው የለ ። ድንጋይ ውርወራ የለ ጎማ ማቃጠል የለ ። መጮህ መሰፏጨት የለ መፈክር ማሰማት የለ በቃ ስልክ ወጣ አድርጎ መደወል ። ተቃውሞውን በጨዋ ደንብ መንገር ። አለቀ በቃ ጉዳዩ እዚያ ላይ ይፈጸማል ። ይቆማል ። በቃ ይሄ መንገድ በጣም ተስማሚና አዋጭ ጉልበትና ጊዜም ቆጣቢ መንገድ ሆኖ አግኝተነዋልና ወደፊት ፋክስና ኤሚዬልን ጨምረን በቤተክርስቲያን ላይ የሚያላግጡትን በሙሉ ልክ እናስገባበታለን ። አከተመ ።
በሌላ በኩል በውጭው ሲኖዶስና በሀገር ቤቱ ሲኖዶስ ስር ተከፋፍለው ይገለገሉ የነበሩ ምእመናንና አንዱ ከአንዱ ጋር በጎሪጥ እንዲተያይ ሁለቱም የሃይማኖታችን ቁንጮና መሪ የሆኑ የእምነቱ መሪዎች በፈጠሩት ስህተት ምክንያት መሆኑን ኢትዮጵያውያኑ ከሚገባው በላይ በቂ ግንዛቤ ያገኙበትና የተለያዩ መግባባቶችም የተፈጠሩበትም ሆኖ አልፋል ። ይሄን የህዝብ ለህዝብ ግኑኝነት እንዴት እናስቀጥል የሚለው ነገር በሁላችሁም ዘንድ መታሰብ ይኖርበታል ። በቀጣይም ሁላችንም በደንብ እንመክርበትና በሁለቱም መካከል ያለውን ፀብ እናበርዳለን ፣ በሁለቱም ጠበኞች መካከል ያሉትን ግሪሳዎች በጋራ እናስወግዳለን ። የሁለቱም ፀብ የሃይማኖት ሳይሆን የሥልጣን ፣ የገንዘብ ፣ የዘር መሆኑን እናውቃለን ። ያውም የትግራይ ልጆችና የጎንደር ልጆች ጠብ ። አለቀ በቃ እውነቱ ይሄው ነው ። እሱን እንደምንም ብለን አብርደን የአንድ ሀገር ልጆችን ባይወዱም በግድ ማስታረቅ ይኖርብናል ። አንድ ስንሆን ነው የሚያምርብን ።
የሚገርመው በአሜሪካ የሚገኙት የተዋህዶ ልጆች በተ ከርስቲያን ሲሄዱ ተለያይተው ፣ ተኳርፈው ይሄዱና የቴዲ አፍሮ ኮንሰርት ሲሆን ግን በአንድ ክለብ ሄደው ኢትዮጵያ ሀገሬ እያሉ ሲያለቅሱ ይውላሉ ። በአመታዊው የእስፖርት በዓል ላይም ካሜራ ለማድመቅ ሲሉ በባንዲራ አሸብርቀው ሲያለቅሱ ፣ ሲደሰቱ ይከርሙና ልክ ቤተክርስቲያን ትዝ ስትላቸው መኳረፍ ይጀምራሉ ። እንግዲህ የሰባኪው ስብከት አንድ ማድረግ አቅቶት ቴዲ አፍሮ ከሆነ አንድ የሚያደርጋችሁ ወደ ፊት ቴዲ አፍሮን ሙሴ አድርገን መላክ አለብን ማለት ነው ። መቼም እንጨት እንጨት ከሚለው ከአሰግድ ስበከት የቴዲ አፍሮ ኢንተርቪ ለዘላለም ከአእምሮ አይጠፋም ። ያውም ከሚገርም የቋንቋ አጠቃቀም ጋር ።
በሌላ በኩል ተሃድሶ የለም ለሚሉና ለተሃድሶዎቹ ሳያውቁ ጥብቅና ይቆሙ ፣ ይከራከሩላቸው የነበሩ ወገኖችም አሁን ጨዋታው ፍንትው ብሎ ወጥቷል ። ታይቷልም ።
ሰሞኑን በጭንቀት ተውጠው የነበሩት ፕሮቴስታንቶችና ተሃድሶዎቹ በሙሉ ዛሬ በየብሎጋቸው ስሜታቸውን መቆጣጠር አቅቷቸው ሲፈነጥዙ መታየታቸው በራሱ ለእኔ ታላቅ ድል ነው ። በአባ ኃይለማርያም እና በአባ ተክለሃይማኖት መሾም የጴንጤ መደሰት ነው እኔን ግራ የገባኝ ። " ተቃጠል ፣ አፈር ብላ ፣ አንተ አሳዳጅ ፣ እርር በል ያሉኝ ጴንጤዎች ብዛታቸው ። ቀይ ግን እነሱን ምን አገባቸው እና ነው እንዲህ ያስፈነጠዛቸው ያልን እንደሆነ መልሱ አለ ነገር ጠርጥር ከገንፎም ውስጥ አይጠፋም ስንጥር የሚለውን አባባል ያስታውሰኛል ። ምድረ ሰገጤ ሁላ.! ፓስተሮች ሳይቀሩ እኮ ነው የጻፉልኝ ፣ የደወሉልኝ ። እኔ ምን አገባኝ ታዲያ እንደ አመጣጣቸው አስተናግጄ መልሻቸዋለሁ።
ሁለቱ ተሿሚዎች ለእኔ በግሌ መልካም ወዳጆቼ ናቸው ። ለዚህም ነው አባ ተክሌ ስለፈሩኝ ወደ አሜሪካ በመደወል ለቀሲስ ንዋይ ካሳሁን እባክህ ዘመዴን ተወኝ በለው በማለት ለአማላጅነት ደጅ የጠኑት ። ፣ ዶር አባ ኃይለማርያምም ከአዲስ አበባ ድረስ ደውለው " ዘመዴ በእመቤቴ ፣ በቅድስት ሥላሴ ብለህ ተወኝ ፤ ያጠፋሁትም ነገር ካለ አስተካክላለሁ ። ከእነ በጋሻውም ጋር ሚሊኒየም አዳራሽ የተገኘሁት ታዝዤ ነው " እስኪሉኝና እስኪያለቃቅሱ ደረስ ያደረሰን የእኔ ድርቅናና ቅድሚያ ለሃይማኖቴ ማለቴ ነው ። እናም ዛሬም እኛ አሸንፈናል ። ጉባኤተኞቹን አስጨንቀናል ፣ አባቶቻችን ስህተት ቢሠሩም አስምጠናቸዋል ፣ ሹመቱ ቀድሞ ያለቀ እና የደቀቀ ፣ የተሿሚዎቹ መጽሔትም ቀደም ብሎ የተዘጋጀ ቢሆንም የግድ የጨነቀ ድራማ እነደዲሠሩ አስገድደናቸዋል ።
ሌላው በእኔ በኩል የየኔታ ዕዝራን መመረጥ ደግፌ አልነበረም እከራከር የነበረው ። ሁኔታው ክብረ ነክ መሆኑ ቢነደኝ ጊዜ ነበር እሪ የምል የነበረው ። በሃገሩ ሰው የሌለ ይመስል ኪዳን ማድረስ የማይችለውን ጓደኛዬን አባ ተክሌን ያለተወዳዳሪ አስቀምጦ ዐራት አይናውን ሊቅ ትምህርቱን በአግባቡ ካልጨረሰና አዘዞ ተወልዶና አድጎ ለስልጣንና ለሹመት ሲል አቡነ ጳውሎስ ትግሬ ነው የሚሾሙት የሚል ነገር በመስማቱ መታወቂያውን በአድዋ የቀየረን የስልጣን ጥመኛ ሰው ከእኚህ ታላቅ የሃገር አድባር ጋር ማወዳደሩ ተገቢ መስሎ ስላልታየኝ ነው ።
አባ ኃይለማርያም ከእኔ ወዳጅ ከብፁዕ አቡነ ጢሞቴዎስ ጋር ነው ቁርስ ምሳ እራት ማዕድ የሚቆርሱት ፣ አቡነ ጢሞቴዎስ ደግሞ እንኳን ጳጳስ ፓትሪያርክ በመምረጥ የሚታወቁና ሁሉን ማድረግ የሚችሉ አድራጊ ፈጣሪ ናቸው ። እናም የዶር መመረጥ የተበላ እቁብ መሆኑ ይታወቅ ነበር ።
የሚገርመው አረጋዊው አባት አቡነ ቀውስጦስ ሳት ብሏቸው የተናገሩትን ነገር እዚህ ጋ ማንሳት ይኖርብናል ። " ዕዝራ ጉበኤውን የት ጥሎ ነው ለጵጵስና የሚወዳደረው ፤ እኛ ዶርን ነው የምንመርጠው እሱን ነው የሚሻል " ብለው መናገራቸው እውነት ነው ። አቡነ ቀውስጦስ ዶክተሩን ይዘው በማኅበረ ቅዱሳን ጉባኤዎች ላይ እንዲሰብክ ይዘው መዞራቸው እና እንዲሰብኩ ማድረጋቸውም የገጽታ ግንባታ መሆኑ ነበር ።
አቡነ ቀውስጦስ ግን እውነት ነበራቸው ። ምክንያቱም የኔታ ዕዝራ ጳጳስ ቢሆኑ ጉባኤያቸው ይፈታል ። ቢሮ ይውላሉ ፣ ተተኪ ይጠፋል ፣ የተተኪዎች ምንጩ ይደርቃል ፣ እንደልባቸው መሆን አይችሉም ። በቁማር የጦዙ ፣ ሃይማኖት የሌላቸውን የአስተዳደር ሰራተኞች ሲዳኙ ነበር የሚውሉት ፣ የኔታ የቁም እስረኛም ይሆኑ ነበር ። የኔታ እኮ በበዓታቸው ተቀምጠው እያስተማሩ ፣ በርካታ ሊቀሊቃውንት ምሁራንን እያፈሩ ለቤተክርስቲያን የሚገብሩ ገባር ወንዝ እኮ ናቸው ። አሁን እንኳ በእንዲህ አይነት ትጋት እያስተማሩና እያገለገሉ በተጨማሪም በትርፍ ሰዓታቸው ደግሞ የሚገራርሙ ታላላቅ መጻሕፍቶችንም ለትውልዱና ለቅድስት ቤተክርስቲያን አበርክተዋል ። እና ምን በወጣቸውና ነው ጉባኤ ፈትተው የእግዚአብሔር መንፈስቅዱስን ትዕዛዝ ጥሶ በመንግሥት እየተጠመዘዘ ጳጳስ ከሚሾም የሲኖዶስ ጉባኤ ምን ይሠራሉ? ምንም አይሠሩም ። ሲኖዶሱ ቀረበት እንጂ እሳቸውማ ምን ሊቀርባቸው ። አረ በማርያም.!!
የዚህ ዘመን ጵጵስና እንደሆነ ብፁዕ አቡነ እንድሪያስን የመሰሉ ተጠያቂውን ፣ ታላቁን ሊቅ ሀገረ ስብከት አልቦ አድርጎ አስቀምጦ አስወግዶ የቁም እስረኛ ያህል በጠቅላይ ቤተክህነት ግቢ ታስረው እንዲቀመጡ ከማድረግ ውጪ ምን ጠቀማቸው ? ስንትና ስንት የቀለም ቀንድ የሆኑ ሊቃውንትን የሚያፈሩ አባት በጎሰቆለ ሁኔታ ፣ ለአንድ ሊቅ በማይገባ መልኩ ቤት ተዘግቶባቸው እንዲውሉ ከማድረግ ውጪ ምን ተጠቀሙ ? ምንም.?
በግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥትም ሆነ በደርግ ጊዜም ቢሆን የጳጳሳት ምርጫ የአገዛዞቹ እጅ ሳይኖርበት ቀርቶ አይደለም ። ያኔም ቢሆን የንጉሠ ነገሥቱን መልካም ፈቃድ ሳያገኙ የተሾሙ ጳጳሰት አልነበሩም ። ደርግም ቢሆን ፓትሪያርክ ያህል በገመድ አንቆ ገድሎ ነው የራሱን ፈቃድ የሚፈጽሙለት መነኮሳትን መርጦ የሾመው ። አቡነ ጳውሎስ ለ10 ዓመት በደርግ እስር ቤት ውስጥ የማቀቁት ደርግ ያለፈቃዴ ፣ እኔ ሳላምንበት ለምን ተሾሙ በማለት አኩርፎ ነው ያሰራቸው ። እንዲያም ሆኖ ግን የሚሾሙት ሊቃነ ጳጳሳት የዘመናዊ ትምህርት ዝግጅት በይኖራቸው እንኳ የቤተክህነቱን ትምህርት ጠንቅቀው የሚያውቁ ነበሩ ። የቤተክህነቱንም ሆነ ዘመናዊውንም ትምህርት ጠንቅቀው የዘለቁና ከሁሉም በላይ በሃይማኖታቸው አንቱ የተባሉና የተመሰከረላቸው ነበሩ ።
ፓትሪያርኩ አቡነ ተክለሃይማኖት በአንድ ቀን ታጭተው ፣ በአንድ ቀንም ተመርጠው ፓትሪያርክ ቢሆኑም ከተሾሙ በኋላ ግን ከመረጣቸው ደርግ ጋር እልህ በመጋባት ብዙ ሥራ የሠሩ አባት ነበሩ ። በረከታቸው ይደርብንና ቅዱስ ፓትርያርኩ ከጾም ብዛት አጥንታቸው ከሥጋቸው ተጣብቆ መሞታቸው ይታወቃል ። እንዲህ ነበር ያኔ ጵጵስና ።
አቡነ መርቆሬዎስም እድለኛ አልነበሩም ። የብሔራቸው ጉዳይ አንዱ ምክንያት መሆኑ እንዳለ ሆኖ ኢህአዴግ ፓትርያርኩን የሾማቸው ደርግ ነው በሚል ምክንያት ገፍቶና አሽቀንጥሮ ከመንበራቸው በማስወገድ የራሱን ሰው አምጥቶ አስቀምጦበታል ። ተመልከቱ ደርግ ፓትርያርክን ያህል ክቡር የሃይማኖት አባት አንቆ ሲገድል ህዝቡ ዝም ጭጭ በማለቱ ይህን የህዝብ ዝምታ በረሃ ሆነው የከታተሉ የነበሩት ህውሓቶች አጋጣሚውን አግኝተው ወደ ስልጣን ሲወጡ የመጀመሪያው እርምጃቸው ደርግ የፈጸመውን መፈጸም ነበርና ውሻ በቀደደው ጅቦቹ ገቡና አቡነ መርቆሬዎስን ከምንገድል ከምትሰደድ ብለው አጣብቂኝ ውስጥ በመክተት ከሀገራቸው እነዲሰደዱ አደረጉ ።
የአቡነ መርቆሬዎስን ከስልጣን መውረድ ተከትሎ ሥርዓቱ የራሱን ሰፈር ልጅ መሾም ይፈልግ ነበርና አቡነ ጳውሎስን ከተሰደዱበት ሀገረ አሜሪካን አምጥቶ 5ተኛው የኢትዮጵያ ፓትሪያርክ እንዲሆኖ ሾማቸው ። የአቡነ ጳውሎስ ዘመን አሁን በስልጣን ላይ ከሚገኙት ከአቡነ ማትያስ ጋር በጭራሽ በምንም መልኩ የማይገናኝ ፣ በፍጹም የተለየ እና የተሻለ እንደ ነበር አሁን ላይ ከሚታየው ነገር በመነሳት መመስከር ይቻላል። አቡነ ጳውሎስ እንደ ሀገር መሪ በወታደር ብዛት ታጅበው ለንግሥ በዓል መምጣታቸውን አግባብ አይደለም ብለን በወቅቱ ብንቃወምም አሁን ላይ ከምር የአባ ጳውሎስ እንዲያ መሆን ለእኔ ተናፋቂ ሆኖብኛል ። ( እኚህ እኮ ጭር ነው ያደረጉን )
ይባስ ብሎ አሁን የሚታየው ነገር ደግሞ ሲመለከቱትም ሆነ ሲያዩት እጅግ የሚያስጠላ ነው ። ሙሰኞች ቤተክርስቲያንን እንደ ግል ኩባንያ ቆጥረው እየዘረፉ ተምነሽነሸው የሚቀመጡባት ፣ ተጠያቂነት ድራሹ የጠፋባት ፣ ምንፍቅና ፣ ነውርና ነቀፌታ የበዛባን አገልጋይ ነን ባዮች እንደ አሸን የፈላንበት ዘመን ሆኗል የእኛ ዘመን ።
አሁን ለለውጥ መነሳት አለብን ። ቤተክርስቲያን የህዝብ ናት ። ያለ ህዝብ ቤተክርስቲያን ምንም ናት ። የቤተክርስቲያን ባለቤቷ ፣ አልባሿ ፣ ንዋያተ ቅዱሳቱን ፣ መጻሕፍቱን ፣ አስራቱንና በኩራቱን በሙሉ የሚያመጡት ምእመናን ናቸው ። በዚሁ ስሜት እጅግ ውስብስብ ቢሆንም እግዚአብሔርን አጋዥ አድርገን ለለውጥ እንነሳ ።
፩ኛ ፦ ከቅዱስ ፓትሪያርኩ ጀምሮ በቤተክርስቲያኒቱ የሥልጣን እርከን ላይ የሚገኙት ማናቸውም አባቶች ሊሰሩልን ፣ ሊባርኩን ፣ ሊቀድሱን ፣ ሊያፅናኑን የተሾሙብን እንጂ ሊሠሩቡን ፣ ሊነግዱብን ፣ ሊዋሹን ፣ ኢንቬስተር ሊሆኑብን ፣ ሊያስለቅሱን ፣ እንደ አንባገነን መንግሥታት በላያችን ላይ አይነኬ አይጠጌ ፣ ሆነው እንደፈለጉ ፣ እንዳሻቸው ሊፈነጩብን አይደለም ። ምእመናን ይህን በደንብ እንወቅ ። እናም እነሱ የሚሉንን እንደምንሰማቸው ሁሉ እነሱም የምንላቸውን ሊሰሙን ግድ ይላል ።
የማንፈልገውን ፣ የማናምነውን ፣ የምንጠራጠረውን ግለሰብ ለምን ይሾሙብናል ፣ እኮ ለምን??? ይሄ መታረም አለበት ፣የምናርመውም እኛው ነን ። እንዴት የሚለውን በቀጣይ እመለስበታለሁ ።
፪ኛ፦ በባንክ ፣ በውልና ማስረጃ ፣ በኢንሹራንስ ውስጥ የምትገኙ የተዋሕዶ ልጆች በሙሉ ። ከድሆች መቀነት ላይ ተፈትቶ ለቤተክርስቲያን አገልግሎት እና ልማት ይውል ዘንድ የተሰጡ ገንዘቦችን በጉልበታቸው በመዝረፍ ሀብት ያካበቱት ሌባ ጸሐፊዎች ፣ አለቆች ፣ ቁጥጥሮች፣ ገንዘብ ያዦች፣ የሀገረ ስብከትና የጠቅላይ ቤተክህነት ሹሞች እንዲሁም የጳጳሳት የገንዘብ መጠን ፣ የንብረት አይነት ፣ መኪና ፣ ቤት ወዘተ መዝግባችሁ ላኩልኝ ። ከዚያ ምን አይነት ውሳኔ እንደምንወስን አሳያችኋለሁ ።
24 ሰዓት በመቅደሱ ቆሞ በምስጋና በመጮህ እግዚአብሔርን የሚያመሰግነው ፣ ምእመናንን በኪዳን ፣ በቅዳሴ ፣ በማኅሌት ፣ በክርስትና ፣ በኃዘን በደስታ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል እንደመላእክት የሚያገለግለው ምስኪኑ የልጆች አባት የሆነው ካህን በሰቀቀን ይኖራል ። እሱ ባገለገለው አገልግሎት ምክንያት የመጣውን ገንዘብ ግን የሚበላው ፊደል ያልቆጠረ እና በጉቦ የተሾመ ተራ ካድሬና መሃይም እልም ያለ ሰገጤ በላተኛ ነው ። እናም የካህናትን መብት እኛው ልጆቻቸው እናስከብርላቸዋለን ። እመኑኝ ይህን ለማድረግ ጊዜው ሩቅ አይደለም ።
ምድረ ስግብግብና ሆዳም ከድሬና ዘራፊ ሁላ መንግሥቱ የሥጋ ዘመዶቹ ፣ የሥራ ባልደረቦቹ እና የጥቅም ተካፋዮቹ ስለሆኑ ህግ እንዳይነካቸው ፣ እንደይጠየቁ ፣ እንዳይከሰሱ ፣ ባልተጻፈ ህግ ፈላጭ ቆራጭ ሆነው ተንደላቅቀውና ምንም ሳይጎድልባቸው በሙዳየ ምጽዋት ገንዘብ የሀረር ሰንጋ መስለው ዘና ፈታ ብለው እንዲቀመጡ ያደረጋቸውን የቀን ጅቦች በሙሉ እናስተፋቸዋለን ። የቤተክርስቲያንን ገንዘብ አይናችን እያየ እንመስመልሰዋለን ። ይሄ ደግሞ መብት ነው። ድንጋይ መወርወር ፣ ድምጽ አውጥቶ መጮህ ፣ ማፏጨት ፣ ኡኡ ማለት አያስፈልግም እንዲያው በዝምታ ፣ እንዲያው በትእግስት ፍጥምጥም ማድረግ ይቻላል ። ይኽን ፓትሪያርኩ በሸገር ሬድዮ ቀርበው አስቸጋሪ ነው ያሉትን ሙሰኛ ሁላ አስቸጋሪነቱን እንፈትሸዋለን ፣ ቡሩስሊ ይሁኑ ሸዋዚንገር እስቲ እናያቸዋለን ። ፌደራል ፖሊስ ከሌባ ጋር እንደሚቆምም እናያለን ።
፫ኛ ፦ እንደ አቡነ ማርቆስና ዶር አባ ኃይለማርያም ያሉ ሰዎች ከእነ በጋሻውና ያሬድ አደመ ፣ የፊደል ሬስቶራንት ባለቤት ከሆነው ከአቶ ኤፍሬም ጋር በመሆን በቅድስት ቤተክርስቲያን ስም የሰበሰቡትን ብር አይናችን እያየ በ53 ሚልየን ብር የከፈቱትን ፋብሪካ ለቤተክርስቲያን እንዲመለስ እናደርገዋለን ። ዶር አባ ኃይለማርያም ገንዘቡን ይዘው ልጆቹ ጠፍተዋል ቢሉም አቡነ ማርቆስ ግን ተካፋይ እንደ ነበሩ ማስረጃዎች አሉ ። እናም ቱ ምናለ በሉኝ የበሏትን በሙሉ እናስተፋለን ።
፫ኛ ፦ ከዛሬ ጀምሮ የመነኮሳትን ልብስ መብሶ በየቡና ቤቶቹ ውስጥ የሚንዘላዘል ዘልዛላ አሰዳቢ ሰካራምና ዘማዊ መነኩሴ ፣ ከህን እና ዲያቆን ካገኛችሁ እነዚህን አሰዳቢ ወራዶች የመጠየቅ ፣ ምንትሠራለህ ብሎ የመሞገት መብት አላችሁ እናም ሰፈራችሁን አሰከብሩ ። ከዚያ ከባሰበትና ከፈነዳ አውልቆ ህዝባዊ ይሁን እንጂ በማንም ለከርሱ ሲል በመነኮሰ ሆዳም መነኩሴ የተነሳ የአባ እንጦንስና የአባ መቃርስ አስኬማ አይዋረድም ። አራት ነጥብ ።
እንግዲህ ከእኛ የሚጠበቀው ምንድነው ያላችሁ እንደሆን ይህን መልእክት የምታነቡ ምእመናን በሙሉ ። በመጀመሪያ በምንገኝበት አጥቢያ በመሄድ የንስሀ አባት እንያዝ ፣ ንስሐም እንግባ ፣ ቀጥሎ መብትን ለመጠየቅ ግዴታ መግባት ያስፈልጋልና በአስቸኳይ የሰበካ ጉባኤ አባል እንሁን ። የሚጠበቅብንን ክፍያም አሟልተን በደብራችን የሰበካ ጉባኤ የአባልነት መታወቂያ እንያዝ ። ክፍያው በጣም ትንሽ ነው ። ያንጊዜ መብት ይኖረናል ። የፈለግነውን ጥያቄ መጠየቅም እንችላለን ። ይሄን ሳይውል ሳያድር ፈጽሙት ።
፬ኛ፦ ወጣቶች በአስቸኳይ ወደ ሰንበት ትምህርት ቤት ግቡ ። ተማሩ ፣ ዘምሩ ። አገልግሉ ። የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች በማኅበረ ቅዱሳን በሚዘጋጀው የግቢ ጉባኤ በመሳተፍ የድርሻችሁን ተወጡ ። የፖለቲካውን ስፍራ አትፍሩት ። ጠጋ በሉት ። ያዙት ። አለቀ ።
እኔ እንዲህ ነው የማስበው ፣ እንዲህ ነው የምመኘው ። አባ ኃይለማርያም ተሾሙ አልተሾሙ አሁን እሱ ላይ እኝኝ ስንል መገኘት የለብንም ። ይህ ሰው መንግሥት አሁንም ላሹመው ካለ ከልካይ የለበትም ። ቢሾምስ ጎንደር ሊሄድ ነው? ማንስ ክህነቱን ያረከሰ ጳጳስ መስቀል ይሳለማል ። ያው ፓርላማ አስገብቶ ቢሮ ካላሰራው በቀር መቼም በህይወት እያለን የሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ አይሆናትም ። ቱ ሞተናታላ ።
አባ ተክለ ሃይማኖትም ቢሆን እኔም ቢሾም ጉዳዬ አልነበረም። ከመሾሙ አይደለም ተቃውሞዬ ። እሱ ግን ውሎው ከእነ በጋሻው ፣ ከእነ መናፍቁ አስራት አያንሳ ጋር ነው። በኮሌጅ አብረው የተማሩትን ኦርቶዶክሳውያን ልጆች መች በአውደምህረቱ ላይ አቁሞ ያውቃል.?? መቱ ከመምህር ምህረተአብ ጋር አፈር ፈጭቶ ያደገው ፣ በሰንበት ትምህርት ቤትም ሲያገለግል የነበረው አባ ተክለሃይማኖት ከመናፍቃኑ ግሪሳዎች ጋር እልም ያለ ፍቅር ውስጥ ወፍቆ ሲዳክር እናይ የለ እንዴ ። 6 አባወራዎች በሚገኙበት ቦታ ሁሉ ቤተክርስቲያን ካልከፈትኩ ማለትና ካህንና አገልግሎት የማይሰጡ ሲቪ ማሳመሪያ ቁጥር ብቻ የሆኑ አብያተክርስቲያናትን መክፈቱ ብቻውን በቂ አይደለም ። እናም በመንግስት ደብዳቤ በግድ የተሾሙት ጳጳስ ካቢኔውን ይባርኩ ካልሆነ በቀር ምን እነደሚሠሩ እናያለን ። ይልቅ መንግሥት ለምን ሰውየው እንዲሾሙለት እንደፈለገ ካስፈለገ ለማውጣት እገደዳለሁ ። እናም በአስቸኳይ ማስተካከያ ይደረግበት ።
በተረፈ ሊቀሊቃውንት የኔታ እዝራ ሀዲስ ፣ እንኳን ደስስ ያሎት ። እንደኔ እንደኔ ሹመቱ አሁን እንደምናየው ሌሎቹም የተሾሙቱ በቀደመው መንገድ በአግባቡ ሥራ ላይ ሲያውሉት አይታይምና እንደኔ እንደኔ ሹመቱ ለእርስዎ ሺህ ሞት ነውና ቢቀርቦት ባይ ነኝ ። ይተውት ፣ ይናቁት ። እነሱ እርስዎን ለማዋረድ እንደደከሙት እርስዎ ደግሞ በተለመደው ፈገግታው ባላየና ባልሰማ ይለፏቸው ። ኪዳን ማድረስ ከማይችለውና ለፖለቲካ መጠቀሚያነት መንግሥት ታንክ አቁሞ ካስመረጠው ከጨዋው አባተክሌ ጋርማ እርስዎ እኩል ብፁዕ አባታችን ተብለው አይጠሩም ። እርስዎ ክብርዎ ከምን እንደሆነ የምናውቅ እናውቀዋለን ። አከተመ ።
ስደተኛውና ሀገር አልባው አክባሪ ልጅዎ
እንኳንም ተሰደድኩ ፣ እንኳንም አስጨንቀው ከሀገሬ አስቀሩኝ ። ስለእውነት እንነጋገር ከተባለ አሁን እንደምፈነጨው በሀገሬ ብሆን እፈነጭ ነበርን? ። መንፈራገጤ አይቀርም ነበር ። ነገር ግን ኮማንድ ፖስቱ ዋጋዬን ሰጥቶ አደብ ያስገዛኝ ነበር ። ወይ አንቀጽ ጠቅሶ ሸዋሮቢት ፣ ወይ ደግሞ አከናንቦ ሰማይ ቤት ይልከኝ ነበር ። አሁን ግን ለጊዜው ሰላም ወረዳ ነው ያለሁት ፤ እናንተ መረጃዎችን ላኩልኝ እኔ እንደሚሆን እንደሚሆን አደርገዋለሁ። እስከ ጊዜው ድረስ ።
" እኔ ግን እላለሁ !!! እምዬ ኦርቶዶክስ አንቺ እናትዓለም ፤ የእነ ቅዱስ ዲዮስቆሮስ ፣ የእነ ቅዱስ አትናቴዎስ እና ቅዱስ ቄርሎስ የእነ ቅዱስ ጊዮርጊስ ፣ የእነ ቅድስት አርሴማ ፣ የእነ አቡነ ተክለሃይማኖት ፣ የእነ አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ፣ የአባ ሳሙኤል ዘዋልድባና የአቡነ አረጋዊ ሃይማኖታቸው የሆንሽ ንጽህት ተዋሕዶ ሃይማኖቴ ሆይ ! ብረሳሽና ብከዳሽ ቀኜም ትርሳኝ፣ ትክዳኝም ። ባላስብሽና ባልሞትልሽ ምላሴ ከጉሮሮዬ ይጣበቅ ። ሳለጎበድድ ሳለከዳሽ እንድኖር አምላክሽ ይርዳኝ ። ይህን ባለደርግና ሳልጮህልሽ ዝም ብዬ ብሞት ስሜ ከህይወት መጽሐፍ ይደምሰስ ።
አንቺ ቅድስት ቤተክርስቲያን ሆይ.! ጌታ በደሙ የመሰረተሽ ነሽና ደሙ ይፍረድልሽ ። አከተመ በቃ.!
"ጌታ ሆይ! ከዚህ በፊት በሆነው ፤ አሁንም እየሆነ ባለው ነገር እና ወደፊትም በሚሆነው ነገር ፤ ክብሩን ሁሉ አንተ ውሰድ ።" አሜን. !
"ድንግል ሆይ እናቴ ! አዛኝቱ ዛሬም እንደትናንቱ ቅደሚ ከፊት ከኋላዬ "
ፌስ ቡክ What's on your mind? ስላለኝ ይህንንም ራሴው ከአእምሮዬ አቅንቼ በእጄ ጻፍኩት ። +4915217428134 የቫይበር ፣ የኢሞና የኋትስአፕ መልእክቶችን የምቀበልበት የእጅ ስልኬ ነው ።
ሻሎም.! ሰላም.!
ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
ግንቦት 11/2009 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ።

አዝማሪ ትዝታው የራሱንና የቤተሰቡን የአንገት ማዕተብ ከበጠሰ ቆየ ።

ግሪሳ ትዝታው ( ሉንጎ )  መቅሰፍት ሊወርድበት  ነው ★ ★ ★ ✔  Share ~ Comment ~ Like ~ Tag ★ አዝማሪ ትዝታው የራሱንና የቤተሰቡን የአንገት ማዕተብ ከበጠሰ ቆየ ። ★በኮሎራዶ.! ...